ብዙዎች
ለኦርቶዶክሳዊት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅርብ የሆኑ እንደሚያውቁት ማህበረ ቅዱሳን የተባለው ማህበር ከምድር
ተነሥቶ ስም ያጠፋል፣ በሰው ነገር እየገባ እርስ በርስ ያጋጫል፣ ይደበድባል፣ ካስፈለገም ይገላል ለዚህ ሁሉ በመቶ
የሚቆጠር ማስረጃ አለን። አሁን እጅግ የከፋውና በጣም አሳሳቢ የሚሆነው ፐርሰናል የሆኑ ጉዳዮችን ወደ አደባባይ
ማውጣቱ፣ የግለሰብን ሕይወት ከትውልድ እስከ ዘር ማንዘር አስተሳሰቡና ጠቅላላ ሕይወቱ እየተሰለለ ለማን እንደሚሰጥ
በማይታወቅበት ሁኔታ ለአደጋ መጋለጡ ነው።
Monday, February 27, 2012
Tuesday, July 26, 2011 ማህበረ ቅዱሳንን ለመምራት የሚሞክር ሥውር አመራር አለ። (ዲ. ዳንኤል ክብረት) - - -
July 26, 2011
(ደጀ ሰላም፤ ጁላይ 26/2011/ READ IN PDF)፦ “ዕንቍ” የተባለ መጽሔት የማ/ቅዱሳን ዋና ፀሐፊ መምህር ሙሉጌታ ኃ/ማርያምን ባነጋገረበት እትሙ ስሙ ያለአግባብ መነሣቱን በመጥቀስ ጉዳዩን ግልጽ ለማድረግ መልስ መስጠቱን ዲ/ን ዳንኤል ክብረት በተለይ ለደጀ ሰላም በላከው ደብዳቤ አስታውቋል። “ዕንቁ
መጽሔት ከማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ ጋር ያደረገውን ቃለ መጠይቅ ማውጣታችሁ ይታወሳል፡፡ በቃለ መጠይቁ ውስጥ
ስማቸው ከተነሡት አካላት አንዱ በመሆኔ ለጉዳዩ ያለኝን የተለየ ሃሳብ በማውጣት እንድትተባበሩኝ እጠይቃለሁ” ያለው ዲ/ን ዳንኤል ዋና ፀሐፊው መምህር ሙሉጌታ ላነሧቸው ነጥቦች የግሉን አስተያየት ከመስጠቱም በላይ እርሱ ከማ/ቅዱሳን አመራር ጋር አለኝ ስላለው አለመግባባት በሰፊው ማብራሪያ አስፍሯል። ደጀ ሰላም “ዕንቍ” መጽሔት ላይ የወጣውን ቃለ ምልልስ ለደጀ ሰላማውያን እንዳቀረበችው ሁሉ አሁንም ዲ/ን ዳንኤል “ለጉዳዩ ያለውን የተለየ ሐሳብ” ታቀርባለች።
መምህር ሙሉጌታ ኃ/ማርያም ከላይ ለተጠቀሰው መጽሔት በሰጡትና በዓይነቱ ለየት ባለው ቃለ ምልልሳቸው ውይይት የሚጋብዙ ቁምነገሮችን የጠቀሱ ሲሆን “እውነቱን ለመናገር አብዛኞቹ የማህበረ ቅዱሳን አባሎች የኢሕአዴግ ደጋፊና አባላት ናቸው” በሚለው ጥቅል ሐሳባቸው ብዙዎች ግር መሰኘታቸውን፣ አንዳንዶችም “ይቅርታ ይጠይቁ” ማለት መጀመራቸው ታውቋል። በቃለ ምልልሱ ከማኅበሩ ቋሚ ሠራተኝነት በመልቀቅ በትርፍ ጊዜው ብቻ በማገልገል ላይ የሚገኘው ዲ/ን ዳንኤል ክብረትን በተመለከተ ተጠይቀው በሰጡት መልስ አነስተኛነት ብቻ ሳይሆን ትክክለኛነት ቅሬታ አለን ያሉ አባላት ጉዳዩን በማንሳት ዋና ፀሐፊውን የሞገቱ ሲሆን በስም የተጠቀሰው ዲ/ን ዳንኤልም በፌስቡክ ገፁ ቅሬታውን ገልጾ አንብበነዋል።
ዲ/ን ዳንኤል “እርምት የሚያስፈልገው መግለጫ” ባለውና ጁላይ 4/2011 በለጠፈው አጭር ማሳሰቢያው “የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ሙሉጌታ ኃይለ ማርያም በዕንቁ መጽሔት ላይ ስለ ማኅበሩ የተናገራቸው አብዛኞቹ ነገሮች መልካም ቢሆኑም፣ እኔን እና ቀሲስ ሰሎሞንን በተመለከተ የሰጠው መግለጫ ግን የማኅበሩንም የክርስትናንም ሕግጋት የጣሰ ነው፡፡ ከዚህም በላይ «አብዛኞቹ የማኅበሩ አባላት የኢሕአዴግ አባላት እና ደጋፊዎች ናቸው» ያለበትም
ምክንያት ምንም ማረጃ እና መረጃ የሌለው ነው፡፡ እስካሁን በማኅበረ ቅዱሳን ታሪክ በከፍተኛ አመራር ደረጃ
የተሰጠ፣ የአባላቱን ፖለቲካዊ ተሳትፎ የሚገልጥ የመጀመርያው መግለጫ ነው፡፡ እኔ በግሌ ይህንን እቃወማለሁ፡፡ ነገ
ደግሞ ሌላው አመራር ተነሥቶ «የቅንጅት አባላት እና ደጋፊዎች ናቸው» ከማለቱ በፊት እርምት ያስፈልገዋል፡፡” ማለቱን አንብበናል።
ማቅ - ስመ ቅዱሳንን የያዘው ማህበር
ስለዚህ ማኅበር አወላለድ በመምህር ጽጌ ስጦታው(ይነጋል) እና በዲያቆን ሙሉጌታ ወ/ገብርኤል (ማኅበረ ቅዱሳን ወይስ ማኅበረ ሰይጣን) መጽሐፍ ብዙ ብዙ ስለተገለጠ ለጊዜው ከዚያ የምጨምረው የለኝም ። ከተወለደበት የዝሙት ህይወቱ ባሻገር አሁን ባለው የገንዘብ አፍቅሮቱና ያልበላውን የሚያክበት የቤተክርስቲያንን ታዛ የተጠለለበትን መሰሪ አካሄዱን በተመለከተ ጥቂት ለማለት እወዳለሁ።
ማቅ መሰሪ የሚባልበት ዋናው ምክንያት በምሁራን እውቀትና ያለእውቀት ጭፍን የክርስትና አፍቅሮት ባላቸው አላዋቂዎች መጠቀም መቻሉ ነው። የቅዱሳንን ስያሜ በለበሰው ማቅ ተሸፋፍኖ እውቀት ባላቸው እና በፍቅረ ክርስትና በሰከሩ ማይማን እንዴት እንደሚጠቀም አንድ ባንድ እንመልከት።
በምሁራን እውቀት መጠቀም፤ ይህ ኃይል ማዕከላዊ የበላይነትንና አንድ ወጥ ተዓዝዞትን ለማስፈን ከአዲስ አበባው የማቅ ማዕከላዊ ቢሮ ጀምሮ በክልል ፤በዞን፤ በወረዳና በአጥቢያ የእስትንፋስ ሴሎችን የሚያዋቅር፤ የሚያደራጅና የሚመራ የኅልውናው አንቀሳቃሽ ዋና ሞተር ነው። ከላይ ወደታች ይተነፍሳል፤ ከታች ወደላይ እስትንፋስ ይቀበላል። የደም መልስና የደም ቅዳ(circulation) ዓይነት ሥራ የሚከውን የማቅ ማዕከላዊ ልብ ነው። ይህ አካል ማዕከላዊ የበላይነትን ሳይሸራርፍ ሌሎች አመላላሽ የደም ሥሮችን ገጥሞ በቤተክርስቲያን ሕይወት ውስጥ ሕይወቱን ያመላልሳል። ይኸውም፣
Subscribe to:
Posts (Atom)