Monday, January 28, 2013

የዳንኤል ክብረት ክሽፈት


ጥር 2005
(አቶ ዳንኤል ክብረት በተለመደ ስሙ ዳንኤል ክስረት የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያምን አዲስ መጽሐፍ አስመልክቶ በጻፈው መደዴ ጽኁፍ ያዘኑት ፕሮፌሰሩ የአላዋቂ ሳሚ ሌላ ነገር እንዳይለቀልቅ ብለው በብሎጋቸው ላይ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ መልስ ሰጪ የለም ብሎ የድፍረት ጽኁፍን እያስነበበን የዘለቀውን አቶ ዳንኤል ከቤተክህነት ተንኮሉን እንጂ ሙያውን ስላልያዘ ፕሮፌሰሩ በትክክለኛ መጠሪያ ስሙ አቶ ዳንኤል ሲሉ ጠርተው ወዳጆቹ ባስቀመጡት ወንበር ላይ ሳይሆን በሚመጥነው ወንበር ላይ አስቀምጠውታል፡፡ ምላሹ ተገቢም ወቅታዊም አስፈላጊም በመሆኑ አንባቢያን እንዲያነቡት እንጋብዛለን፡፡ መልካም ንባብ)

አቶ ዳንኤል ለመናገርና ለመጻፍ ያለው ፍጥነት በሚናገርባቸው ጉዳዮች ላይ ካለው እውቀት ጋር አይመጣጠንም፤ እንዲያውም ያውቃል እንዲባል የሚጽፍ አንጂ አውቆ የሚጽፍ አይመስልም፤ አቶ ዳንኤል ሳላውቀው በጻፈው ላይ አስተያየት ስሰጥ ይህ ሁለተኛዬ ነው፤ ከዚህ በፊት በአንድ ጋዜጣ ላይ በጣም የታወቀውን የአየርላንድ ችጋር 150 ዓመታት ያህል አቅርቦት በማየቴ አስተያየት ሰጥቼበት ነበር፤ ዛሬ ደግሞ ስለመክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ በጻፈው ላይ አጭር አስተያየት ልስጥ፤ እንዲያው እንትንን እንትን ካላሉት ገብቶ ይፈተፍታል የሚባለውን በመከተል እንጂ ትርፍ ይኖረዋል ብዬ አልገምትም፤ ከደርግ ዘመን ጀምሮ የተለያዩ ካድሬዎች ደብተራዎችም ጭምር ማነብነብን እንደተናጋሪነት ሠልጥነውበታል፤ ስለዚህም ሰውም ማነብነባቸውን እንደእውቀት እየወሰደው ይወናበዳልና በጊዜው መልስ መስጠት ግዴታ ይመስለኛል፤ የሰው ልጅ በምን ይታፈራል? በወንበር፤ በወንበር አይደለም በከንፈር፤ ይባላል፡፡
ነገር ሳላበዛ ጥቂት ነጥቦችን በማንሣት የአቶ ዳንኤልን የማንበብ ችሎታና የተንኮል ክህነት ብቻ ለአንባቢዎች ላሳይ፤ ስለአስተያየቱ አስተያየት መስጠት አስፈላጊ አይደለም፡፡

Sunday, January 27, 2013

ካህን ይመራሃል እንጂ አይከተልህም!

Read in PDF:kahene
በዲ/ ሙሉጌታ ወልድገብርኤል
የጽሑፉ ዓላማ:
ምንም አንኳን ለሺህ ዘመናት አብረው ቢኖሩና አሁንም አብረው ቢመላለሱ ዳሩ ግን በሚገባ ያልተዋወቁ
በኢትዮጵያ የክርስትና እምነት ተከታዮች ምእመናንን አግብርተ እግዚአብሔር ከሆኑ እውነተኛ የእግዚአብሔር ካህናት ጋር ለማስተዋወቅ ተጻፈ።
ማሳሰቢያ:
በዋናነት በጽሑፉ ለማስተላለፍ የተፈለገው መልእክት ምእመናን እንደ አማኞችና ተከታዮች መጠበቅ የሚገባቸው ዋኖቻቸውን ይለዩና ክብር ለሚገባቸውም የሚገባቸውን ክብር ይሰጡ ዘንድ ተጻፈ እንጅ በክህነት ስም በቤተ ክርስትያን የመሸገውን ሰርጎ ገብ ወረበላ ሁላ እንዳሻው ይናጣችሁ የሚል መልዕክት የለውም:: ይህን ይሆን ዘንድም አልጻፍኩላችሁም።
በተጨማሪም ጽሑፉ በይዘቱ ኑሮ ለመሸወድ ተመሳስለው የተቀላቀሉ፣ ሁሉን በሚያውቅ በእግዚአብሔር ፊት መንዳቢያንሳሉ በሰው ዘንድ እንደ መጋቢያን የሚታወቁና እንደ መጋቢም የሚጠሩ፣ "አባ/አቡነ እገሌ" ተብለው በሚጠሩ ጊዜም "አቤት" ለሚሉ መነኮሳት አይመለከትም። እውነተኛ ካህን ሲጠራ አቤት አይልም አይደለም አንድምታው ቁምነገሩ ያለው ወዲህ ነው። ያዕቆብ በስጋ ወላጅ አባቱ ከሆነው ከይህሳቅ ዘንድ እንዴት ምሩቃት እንደወሰደ እናውቃለን። ያዕቆብ ከአባቱ ምርቃት የወሰደበት መንገድ ትክክለኛ በሆነ መንገድ ሳይሆን ወንድሙን በመምሰልና በአባቱ ፊትም በቀረበ ጊዜም ያዕቆብ ሳለ ኤሳው ነኝ በማለት አባቱ በማታለል ነበር ምርቃቱን ሊያገኝ የተቻለው። ታድያ ከዕለታት አንድ ቀን ያዕቆብ እግዚአብሔር ፊት ቀርቦ ነበር እግዚአብሔርም ይባርከው ዘንድ "ስምህ ማነው?” ባለው ጊዜ በአባቱ ላይ ያደረጋትን የማታለል ድርጊት በእግዚአብሔር ፊት አልሞከራትም። ለማስተላለፍ ተፈለገው መልዕክት ይሄ የሚያምነው የማያውቅ፣ ድግስ የማያመልጠው፣ እንደ ወርሀ መስከረም ዝንብ በዙሪያችን የሚያንጃብበውና ለሰውም "ለእግዚአብሔርም" ፈተና የሆነ ከማደሪያው ኮብልሎ ለከተመ "ፈላሲ" አይመለከትም ነው።