Friday, November 30, 2012

ማኅበረ ቅዱሳን በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ውስጥ «ብላክ ማርኬት» እንዳለው ተሰማ


ምንጭ አባ ሰላማ

(ማሕበረ ቅዱሳን የተባለው የትናንሽ ጋኔኖች ስብስብ የሚሰራውን አሳጥቶ እያቅበዘበዘው ነው፡፡ ህልማቸው ሀሳባቸው እንቅስቃሴያቸው እና ግባቸው ሁሉ ገንዘብ ብቻ የሆነው እነዚህ ሰዎች እልል በቅምጤ ብለው ዶላር መመንዘር ያውም በቤተክህነት ግቢ ውስጥ መጀመራቸው ይደንቃል፡፡ ለምሩቃኑ ተስፋ ነው የተባለው የምሩቃኑ ስብሰብ እንደ ማንዘዋል ባለ የማቅ አለሌ ወታደር ከተያዘ ወዲሕ ተማሪዎቹን ረስቶ ማኅበረ ቅዱሳንን በጥፍሩም በጥርሱም ማገልገል ከጀመረ ሰነበተ፡፡ አቡነ ጢሞቴዎስ ከግቢው ውጡልኝ ብለው ከቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ከተባረሩ ወዲህ በቤተክህነት ቅጥር ጊቢ ውስጥ ባገኙት ቢሮ የማኅበረ ቅዱሳን ወግ የሚሰለቅበት እና የማኅበረ ቅዱሳን ስራ የሚሰራበት ሆኗል፡፡ አሁን ደግሞ ግቢው ባለቤት እንደሌለው መነግስትም እንደማቆጣጠረቅ አውቀው ብላክ ማርኬት መስራት ጀምረዋል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ለሚያቅደው መንገስት የመመስረት ህልሙ ብላክ ማርኬት ጥሩ የገቢ ማግኛ ስልት ነው፡፡ መንገስት አን ይሄን ደርሶበት እርምጃ ልውሰድ ቢል በለመደ አፋቸው በደጃ ሰላም ላይ መንገስትን በሀይማኖት ጉዳይ ጣልቃ ገባ ሊባል ነው፡፡ መልካም ንባብ)

ድብቅ አላማ ይዞ በሃይማኖት ሽፋን የሚንቀሳቀሰው ማኅበረ ቅዱሳን በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ውስጥ ህገወጥ የውጭ ምንዛሪ ቢሮ በድብቅ መክፈቱን ምንጮቻችን ገለጹ፡፡ እንደ ምንጮቻችን ከሆነ ማኅበሩ ለዚህ ህገወጥ ተግባር የሚጠቀምበት ቢሮ በስም «የቲዎሎጂ ምሩቃን ማኅበር» እየተባለ የሚጠራውና የቲዎሎጂ ምሩቃን በአባልነት የሌሉበትና ማንያዘዋልን ጨምሮ ጥቂት የማቅ «የቲዎሎጂ ምሩቃን» አባላት የሚገናኙበት ቢሮ ነው ብለዋል፡፡ ቢሮው ቀድሞ ከነበረበት ከቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ እንዲወጣ ከተደረገ በኋላ ማኅበረ ቅዱሳን በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ውስጥ ቢሮ እንዲያገኝ አድርጓል፡፡ ይህን ያደረገውም የውጭ ምንዛሬውን ጨምሮ ሌሎች ድብቅ ስራዎችን ለመስራትና ለመጠቀም አስቦ እንደሆነ ምንጮቻችን ይናገራሉ፡፡ ቢሮው የማቅ ሌላው ቢሮ ነው እያሉም ነው፡፡ ማኅበሩ የዶላር ዩሮና ፓውንድ ምንዛሬዎችን የሚያካሂደው በድብቅ ሲሆን ከውጪ አገር ዶላር ይዘው የሚመጡና ዶላር የተላከላቸው የማኅበሩ አባላትና አንዳንድ ጳጳሳትም ዶላር ዩሮና ፓውንድ በዚሁ ቢሮ እንዲመነዝሩ እንደሚደረግ የደረሰን መረጃ ያመለከታል፡፡ መንግስት የዶላር እጥረት አጋጥሞኛል በሚልበት በዚህ ወቅት ማቅ እንዲህ እያደረገ መሆኑ ጉዳዩን አነጋጋሪ አድርጎታል፡፡

Wednesday, November 28, 2012

እናያለን ትላላችሁ እንጂ ዕውሮች ናችሁ!

Read in Pdf: Enayalen
በዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል

ዕለታዊ፣ ሰሙናዊ: አልፎ አልፎም ወርሐዊና ዓመታዊ የዜጎች መውጫና መግቢያ የሚይዙ መነጋገሪያ አጀንዳዎችና ርእሰ ጉዳዮች ዛሬ ብቻ ሳይሆን በየትኛው ዘመን ያለ፣ የሚታይና የሚነሳ ነገር ነው። የዛሬ ሁለት ሺሕ ዓመት በእስራኤል ምድር ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኖ ጥቂቶች የማይባሉ ጸጉር ያስነጨና ፊት ያስቧጨረ ወደ አንድ ጉዳይ ላምራችሁ።
"በዚያን ጊዜ ኢየሱስ በሰንበት ቀን በእርሻ መካከል አለፈ፤  ደቀ መዛሙርቱም ተራቡና እሸት ይቀጥፉ ይበሉም ጀመር ፈሪሳውያንም አይተው እነሆ፥ ደቀ መዛሙርትህ በሰንበት ማድረግ ያልተፈቀደውን ያደርጋሉ አሉት። እርሱ ግን እንዲህ አላቸው፦ ዳዊትና ከእርሱ ጋር የነበሩት በተራቡ ጊዜ፥ እርሱ ያደረገውን፥ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደገባ ካህናትም ብቻ እንጂ እርሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት ሊበሉት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕቱን ኅብስት እንደ በላ አላነበባችሁምን? ካህናትም በሰንበት በመቅደስ ሰንበትን እንዲያረክሱ ኃጢአትም እንዳይሆንባቸው በሕጉ አላነበባችሁምን? ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ከመቅደስ የሚበልጥ ከዚህ አለምሕረትን እወዳለሁ መሥዋዕትንም አይደለም ያለው ምን እንደሆነ ብታውቁስ ኃጢአት የሌለባቸውን ባልኰነናችሁም ነበር። የሰው ልጅ የሰንበት ጌታ ነውና።"

Monday, November 26, 2012

‘ማልደራደርበት ‘ማልቀብረው እውነት አንገት ‘ማያስደፋኝ የማላፍርበት ኢየሱስ የሚለው ስም እስትንፋሴ ነው እውነቱ ይሄው ነው


 Read in PDF: Malederaderebt
እነዚህ ስንኞች የተወሰዱት ከአንድ የግጥም መድበል ውስጥ እንዳይመስላችሁ፤ ዲ/ን ትዝታው ሳሙኤል ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን እና ዘማሪት ዘርፌ ከበደ በጋራ ከሳተሙትና «አለው ነገር» የሚል ርእስ ከተሰጠው የዝማሬ ሲዲ ላይ የተወሰደ ነው፡፡ እውነት ነው ኢየሱስ የሚለው ስም ለእውነተኛ ክርስቲያን እስትንፋስ ነው፡፡ አንገት የማያስደፋና የማያሳፍር የማይቀበርና ለድርድር የማይቀርብ ስም ነው፡፡ እውነትም ኢየሱስ በሚለው ስም ላይ ድርድር የለም!!!


ይህ የዝማሬ ሲዲ ጥቅምት ወር መጨረሻ ላይ ጀምሮ ለምእመናን ቀርቧል። በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ አድባራትና ገዳማት በየበአላቱ ቀን ሞንታርቦ በያዙ ሚኒባሶችና በየመዝሙር ቤቱ ሁሉ እየተሸጠ መሆኑንና ታክሲ ውስጥ፣ በተለያዩ ንግድ መደብሮችና በየካፌውና ሬስቶራንቱ ሁሉ እጅግ እየተደመጠ ይገኛል፡፡ 12 ዝማሬዎች የተካተቱበት ይህ የዝማሬ ሲዲ በውስጡ አስሩ ጌታን የሚያከብሩ፣ ፍቅሩን የሚሰብኩ፣ አዳኝነቱን የሚያውጁና የሚማጸኑ፣ ፈራጅነቱን የሚያዘክሩ፣ ወደንስሀ የሚመሩና መሰል መልእክቶችን ያካተተ ሲሆን ለእመቤታችን ለማርያም የቀረቡ ሁለት ዝማሬዎችም አሉበት። የዝማሬዎቹን ግጥምና ዜማ የደረሱት ደግሞ አብላጫውን መጋቤ ሐዲስ በጋሻው ደሳለኝ ሲሆን በመቀጠል ዲ/ን ትዝታው ሳሙኤል እንዲሁም ዘማሪ ሀብታሙ ሽብሩ አንድ ዜማ መድረሱን ስቲከሩ ያስረዳል። 
  

የደሴ ተክለ ሃይማኖት ምዕመናን "ተስፋዬ ሞሲሳን ያያችሁ ወዲህ በሉን" እያሉ ናቸው

Read in PDF:Yedese Tekelehaymanote
ምንጭ ፡-http://dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com
  • የማኅበሩ አባላት ሌሎችን በሚኮንኑበት የንቅዘት ችግር መጠለፋቸው ዝንጀሮ የራሷን መቀመጫ ካለመመልከቷ ጋር የሚነፃፀር ነው
  • ንቅዘት የዘመኑ የቤተክርስቲያናችን ዋነኛ ችግር ሆኗል
  • ከዚህ በታች የቀረበውን ዘገባ የምትጠራጠሩ ካላችሁ ራሱን ተስፋዬንና በዚህ ዘገባ ስማቸው የተጠቀሱትን በተለይ የደሴ የገዳማት አለቆችንና የቤተክህነት ባለሥልጣናትን ጠይቁ፡፡
 የዛሬ ስድስት ወራት ገደማ ግንቦት 12/2004 . ዝቅተኛ ገቢ ባላት የደሴ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን የገቢ ማሰባሰቢያ መንፈሳዊ ጉባዔ ለማካሄድ ከሳምንታት ቀደም ብሎ ዝግጅቱ ቀጥሏል፡፡ አንድ የቤተክርስቲያን ልጅ፣ የተክልዬ ወዳጅ  የጉባዔውን ሙሉ ወጪ ለመሸፈን ቃል ገባ፡፡ ቃል መግባትም ብቻ ሳይሆን ከአዲስ አበባ ሰባክያንንና ዘማርያንን ጋብዙበት ብሎ 20 ሺህ ብር ለገሠ፡፡ የደብሩ የስብከተ ወንጌል ክፍል ሠራተኞችም ብሩ በእጃቸው ይግባ እንጂ የትኛውን ሰባኪ፣ የትኛውን ዘማሪ እንደሚጋብዙ አልተዘጋጁበትም፡፡ የጥቂቶቹን አገልጋዮች ስም የሚያውቁ ቢሆንም እንኳን የስልክና የመኖሪያ አድራሻቸውን አያውቁትም፡፡ ስለዚህ በአዲስ አበባ የሚኖረውን የሀገራቸውን የወንዛቸውን የደሴውን ልጅ በላይ ወርቁን ያገኙትና ለግንቦት 12 መንፈሳዊ ጉባዔ እያዘጋጀን ነው፤ ግን አገልጋዮችን ስለማናውቃቸው በአንተ በኩል ብታፈላልግልን ይሉታል፡፡
በላይ ወርቁም ሰባኪ ሲባል በዓይነ ኅሊናው የመጣለትን የጥቅም ተጋሪው ተስፋዬ ሞሲሳን አስቦ እሺ ችግር የለውም አገናችኋለሁ ይልና ተስፋዬን ያገናኛቸዋል፡፡ ሰዎቹ መቼም በበላይ በኩል የመጣ ያውም በቤተክርስቲያን ጉዳይ ችግር የለውም በማለት ሙሉ እምነት ጥለውበት ተስፋዬ ራሱንና ሌሎቹንም አገልጋዮች ይዞ እንዲመጣ ይነግሩትና ለትራንስፖርትና ልዩ ልዩ ወጪ መሸፈኛ የሚሆን 20 ሺህ ብሩን አስይዘውት ወደ ደሴ ተመለሱ፡፡
ከቀናት በኋላ በደሴ ተክለ ሃይማኖት ደብር የሚካሄደው ዝግጅት ተጠናቆ ጉባዔው የሚጀምርበት ሰዓት ላይ ተደረሰ፡፡ ይሁን እንጂ፣ በዕለቱ ተስፋዬና ሌሎች አገልጋዮች ይመጣሉ ተብሎ ቢጠበቁ፣ ቢጠበቁ ሳይመጡ ቀሩ፡፡  ተስፋዬን የበላው ጅብ አልጮኽ አለ፡፡ ራሱንም ስልኩንም ሸሽጎ እስከናካቴው ጠፋ፡፡ ወይ እርሱ አልመጣ ካልተመቸው ደግሞ ብሩን አልመለሰ፣ ተስፋዬ አዲስ አበባ ላይ ቁጭ ብሎ ብሩን ይቆረጥመዋል ተብሎ ሳይገመት እንደዋዛ፣ እንደ በረሃ አሸዋ ብሩን አሰረገው፡፡

Sunday, November 25, 2012

ምነው? ኢሳትን ኸይ! የሚል ጠፋ?



 በዲ/ን ሙሉጌታ ወልደ ገብርኤል
በተጠቃሹ "የዜና" ማሰራጫ ማዕከል ስራዎች ዙሪያ ስጽፍ ይህ የመጀመሪያዬ አይደለም። በተለያዩ ጊዜያት ማዕከሉ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን በተመለከተ የሚያሰራጫቸው ሚዛናቸው የሳቱና ግልጽነት የሚጎድልባቸው ዘገባዎቹንና ሐተታዎቹን በማስመልከት ተደጋጋሚ ጽሑፎች ለንባብ መብቃታቸው የሚታወስ ሆኖ በርካታዎቹ ሃያ አራት ሰዓት በማይሞላ ጊዜ ውስጥ ከስፍራቸው እየተነቀሉ ለአንባቢያን እንዳይደርሱ ተደርገዋል።
 ይህ በእንዲህ እንዳለ የዜና ማሰራጫ ማዕከሉ ግድፈቶቹን አምኖ ራሱን ከማስተካከልም ይልቅ  "ሰምቶ ማሳለፍ!” የሚልዋትን ፖለቲካ ተጋርቶ ባለበት ሲረግጥ እየተስተዋለ ነው። እውነት ነው የሕዝብ ጆሮና ዓይን መሆን ማለት "የሕዝብ ጆሮና ዓይን ነን!”  በማለት የመፎከር ያክል ቀላል ነገር እንዳይደለ አንድ የሰከነ ባለ አእምሮ ሰው የማይስተው መሬት የረገጠ እውነታ ለመሆኑ የሚያከራክረን አይመስለኝም።
አንድ መገናኛ ብዙሐን ራሱን በፈለገው መልክና ቅርፅ እየቃኘ ማስተዋወቁ አያጣላንም፤ የጽሑፉ ዓላማም አይደለም። በጥቅሉ ከስሙ ባሻገር በተገለጠው ፍሬው/በስራዎቹ አይጠየቅበትም ማለት ግን አይደለም።

Sunday, November 18, 2012

አባ ሰረቀ ብርሃን እርቀ ሰላሙን አስመልከተው ለሲኖዶሱ ደብዳቤ ጻፉ

Read in PDF: Aba Serke
Read in PDF:Aba Sereke letter to sinodos


አባ ሰረቀ ብርሃን የእርቀ ሰላሙ ጉዳይ ልዩ ትኩረት ይገባዋል ሲሉ ለሲኖዶሱ ደብዳቤ ጻፉ፡፡ አባ ሰረቀ ብርሃን በደብዳቤያቸው “ሁላችን እንደምንገነዘበው ዛሬ ቤተክርስቲያናችን በተለያዩ ኃይሎች በተከበበችበት ወቅት ከማንኛውም በፊት አንድነቷን በሚገባ ማጠናከርና ከሁሉ በፊትም በመካከልዋ የተከሰተውን መለያየት ማስወገድ ቅድሚያ ልትሰጠው ይገባታል።” በማለት በተለይ በዚህ ጊዜ እርቁ ከፍተኛ ትኩረት ሊደረግበት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
“በውስጥም ሆነ በውጭ ያለነው የቤተክርስቲያናቸን ባለድርሻ አካላት ሁላችን የየራሳችንን ክብርና ጥቅም በመተው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክቡር ደሙ የዋጃትን ቅድስት ቤተክርስቲያን ለመጠበቅና የተሰጠንን አደራ እስከ መጨረሻ በብቃት ለመወጣት ከመቼም በበለጠ መልኩ በዚሁ ዙርያ ልዑል እግዚአብሐርን ደጅ በመጥናት ልንሠራ ይገባናል።” ሲሉ የገለጡት አባ ሰረቀ እርቁን ለማደናቀፍ እንደ እባብ ውስጥ ውስጡን እየተሸለኮለኩ ሴራ የሚሸርቡትን የማኅበረ ቅዱሳን አባላት እና መሰሎቻቸውን “ዕርቀ ሰላሙ እንዳይሳካ የሚጥሩና እንዲሁም የቤተክርስቲያኒቱንም ሊቃውንት በማሳደድ ላይ የሚገኙ አካላት ሁሉ ቆም ብለው ሊያስቡ ይገባል፡፡” በማለት መክረዋል፡
ለበርካታ አመታት በሰንበት ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ ሆነው የሰሩት እና ቤተክርስቲናቸውንም አገራቸውንም በእጅጉ የሚወዱት አባ ሰረቀ ብርሃን የሰንበት ማደራጀውን እንቅስቃሴ በተሻለ ደረጃ ለማሳደግ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ በጎ የማይስማማው እና ሁሉን ንጄ እኔ እንደ አዲስ ልገንባው የሚለው ማኅበረ ቅዱሳን በመንገዳቸው ላይ እንደ ዐለት ተደንቅሮ የተለያየ ሰንካላ ምክንያት በመደርደር አላሰራ ይላቸው እንደ ነበር ይታወቃል፡፡ 

Saturday, November 17, 2012

የጉጂ ቦረና ሀገረ ሰብከት ጉዳይ መንግስትን አሳስቦታል፡፡

Read in Pdf:menegesete gugiborena Asasebotal
በማህበረ ቅዱሳን ምክንያት ችግር ውስጥ ከገባ ሁለት ዓመት የሞላው የጉጂ ቦረና ሀገረ ስብከት ችግሩ እየሰፋ እና እየከረረ በመሄዱ መንግስት ቤተ ክህነት አስቸኳይ መፍትሔ እንድትሰጥበት ቢወተውትም ቤተክህነቱ ግን ከአቡነ ጳውሎስ እረፍት በኋላ በጽንፈኛው ማኅበረ ቅዱሳን እጅ በመውደቁ በማኅበረ ቅዱሳን መንገድ ካልኆነ  በቀር ሌላ መንገድ የለም የሚል ልብ አይገቤ ምክንያት ላይ በመወጠሩም መንገስት ችግሩ ከፍቶ ሌላ ነገር ከመከሰቱ በፊት የሚያጣራ የራሱን አጣሪ ኮሚቴ ልኳል፡፡
ካለፈው እሮብ ጀምሮ የማጣራት ስራውን የጀመረው አጣሪ ኮሚቴ ስራውን በተገቢ ሁኔታ እያከናወነ ሲሆን አብሮ ይሄዳል ተብሎ ታስቦ የነበረው በተስፋዬ የሚመራው የቤተክህነቱ ቡድን ግን በተለያዩ ተልከሻ ምክንያቶች የማጣራት ሂደቱን በማዘግየቱ ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት እና ከፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የተወከሉ አጣሪዎች ብቻቸውን የማጣራት ስራውን ቀጥለዋል፡፡

Friday, November 16, 2012

ሰንበት ት/ቤት ወይንስ ያዛውንቶች ክበብ

Read in PDF:Shakiso
ከይሔነው እውነቱ
የሻኪሶ ቅድስተ ማርያም ሰንበት ት/ቤት የተመሰረተው በ1976 ዓ/ም ሲሆን የተመሰረበትን 29ኛ ዓመት በቅርቡ አክብሯል:: ነገር ግን ይህ ሰንበት ት/ቤት እንደ ማቱሳላ የዕድሜ ታሪክ ብቻ ነው ያለው፡፡ ምክንያቱም ሰንበት ት/ቤቱ የማቅ ጥገኛ በመሆኑ ነው ማቅ ለኔ አካሄድ ይመቹኛል ያላቸውን ካስቀመጣቸው 10 ዓመታት አልፏቸዋል፡፡ በቃለ አዋዲው መሰረት እድሜያቸው 30 ዓመት በታች የሆኑትን ወጣቶች በሰበካ ጉባኤ አማካኝነት ያስመርጣል፡፡ በሻኪሶ ግን እንዲህ አይደለም፡፡ ከማህበረ ቅዱሳን በሚተላለፍላቸው ቀጭን ትዕዛዝ የማቅ ቅጥረኞት ተግባራዊ ያደርጋሉ፡፡ እነዚህ ስልጣንን በሞኖፖል ይዘው ወጣቶችን በመጫን ከኪነ ጥበብና ከማርታ መዝሙር ውጪ ቢዘምሩ ይባረራሉ፡፡ 

ይህ የአዛውንቶች ስብስብ መመሪያ የሚወጣውና የሚረቀው በተመረጡ በከተማ ባሉ መኖሪያ ቤቶች ነው፡፡ ለአብነት ያህል በአቶ ልንገረው መኮንን/መፃጉ/ ቤት በአቶ ዘላለም እርቅይሁን በአቶ አዳነ ኪሮስ በአቶ አዳነ ኤዴዬ በመገኘት በማቅ በበላይ ጠባቂ በሆኑት በመርጌታ ሰለሞን ባራኪነት ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ዝማሬን ይቃወማሉ ወንጌል እንዳይሰበክ የወንጌል ተባዮች ናቸው ቤታቸው ውስጥ ግን የሚመለከቱት የዝሙት ፊልም የሚያዳምጡት የአስቴር እና የጥላሁንን ዘፈን ነው፡፡ በአንድ ወቅት የሰንበት ት/ቤቱ ሊቀ መንበር የማቅ ስመ ፅድቅ ጋዜጣ ሪፖርተር ኃብተ ገብረኤል ታደሰ/ቃንጫን/  ቃለ መጠየቅ አድርጎለት ኃብተ ገብርኤልም ሲመልስ ይህ ሰንበት ት/ቤት ጠንካራ ነው ጥንካሬውም ተሀድሶዎችን አናስገባም ብሎ ወጥሮ የያዘ ነው፡፡ እኛ ሳንሱር ሳናደርግ  ማንኛውም ዝማሬ አይዘመርም፡፡ ማቅ ከአዋሳ ማዕከል ከላከልን ዝማሬ ውጪ አናዘምርም፡፡ ለመሆኑ ዝማሬን መቃወም ጥንካሬውን ይገልጣል እንዴ? ወጣቶችን ከቤቱ በማሳደዳቸው ነው ጥንካሬው? ዕድሜቸው ከ45 ዓመት በላይ ስለሆነ ነው እንዴ ጥንካሬያችሁ? ከአንድም ስድስት እህቶች አርግዘው ሲወጡ የት ነበራችሁ? ሱሪ አደረገች ጥፍር ቀለም ተቀባች ብላችሁ ከቤቱ በማስወጣታችሁ ነው እንዴ ጥንካሬው? የናንተን የስጋ ፍቃድ ስላልፈፀሙ ከቤቱ የተባረሩት ቤት ይቁጠራቸው ወላጅ እኮ ልጁን ቤተ ክርስቲያን የሚልከው በወንጌል ቃል በዝተው በዝማሬ ረክተው እንዲመለሱ እንጂ በዲቃላ በዝተው በዝሙት ረክተው እንዲመለሱ እኮ አይደለም!! እናንተ ራሳችሁን ሊቃውንት አድርጋችሁ የተቀመጣችሁ የልምድ አዋላጆች ዝናብ የማይታይባችሁ ደመናዎች ምንጭ የሌላቸው የውኃ ጉድጓዶች እስቲ ጎረቤታችሁን ክ/መንግስትን ተመልከቱ ከ20 በላይ የወንጌል መምህራንን ያፈራ በዓመት ከ4 ጊዜ በላይ ታላላቅ ጉባኤያትን በማድረግ በየሰንበት ት/ቤቱ ኮርስ በመስጠት እኮ ነው የወንጌል አብዮት የፈጠራቸው እንጂ ሐመርና ስመአ ፅድቅ ጋዜጣ የተገኘ ፍሬ አይደለም፡፡

Wednesday, November 14, 2012

በአየር ጤና ኪዳነ ምሕረት የ"ማኅበረ ቅዱሳን"ና የአባ ናትናኤል ፍጥጫበአየር ጤና ኪዳነ ምሕረት የ"ማኅበረ ቅዱሳን"ና የአባ ናትናኤል ፍጥጫ



ምንጭ፡- http://dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com
·        ከአዲስ አበባ እስከ ሀዋሳ የተዘረጋው የሙስናና የአፈና መረብ ዓይነተኛ የ"ማቅ" አደገኛ ባህርይ ማሳያ ነው

·        ከ"ማኅበረ ቅዱሳን" ጋር የሚደረገውን ትግል የአየር ጤና ሕዝብ ተረክቦታል

በምደባም ይሁን በዝውውር ወደ አዲስ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ለሚመጡ እንደ መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ናትናኤል መላኩ ላሉ አስተዳዳሪዎች የሚያጋጥማቸው አማራጭ ሁለት ነው፡፡ አንደኛው አማራጭ በሙስና በተጨማለቀ ብልሹ አስተዳደር ውስጥ ገብቶ በመጠቃቀም ፖሊሲ ከ"ማኅበረ ቅዱሳን" ጋር በሠላም መኖር ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ቃለ ዐዋዲው በሚያዘው መሠረት ለእግዚአብሔርና ለቤተክርስቲያን በቅንነት አገልግሎ ከማቅ የሚመጣውን ጠብ በፀጋ መቀበል፡፡

አባ ናትናኤል ወደ አዲስ አበባ አየር ጤና ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ተዛውረው ሲመጡም የተቀበሉት አማራጭ ሁለተኛውን ነው፡፡ በዚህም ሳቢያ አባ ናትናኤል እግራቸው አየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢን ከረገጠበት ዕለትና ሰዓት አንስቶ "ማኅበረ ቅዱሳን" እርሳቸውን ለማስነሳት ያልበጠሰው ቅጠል፣ ያልማሰው ሥር፣ ያልፈነቀለው ድንጋይ የለም፡፡

Monday, November 12, 2012

የአክሱም ህዝብ እና ካህናት አጣሪ ኮሚቴውን አባረሩ

Read in PDF:Akesum
በጥቅምቱ የሲኖዶስ ስብሰባ አቡነ ሰላማ ለስራ ስለአልተመቹን ይነሱልን ሲሉ አቤቱታ ያቀረቡትን የአክሱም ምዕመናን እና ካህናትን አቤቱታ ቸል በማለት የአክሱምን ንቡረ ዕድ ከቦታቸው እንዲነሱ እና አጣሪ ኮሚቴ ወደ ስፍራው እንዲሄድ የተወሰነው ውሳኔ  ያሳዛናቸው የአክሱም ምዕመናን እና ካህናት በጉድ ሙዳዮቹ አለቃ በአቡነ አብርሃም የሚመራውን “አጣሪ ኮሚቴን” ምን ልታደርጉ መጣችሁ አባቶቻችን ስላልሆናችሁ አንፈልጋችሁም ሲሉ አባረሩ።
“ህዝብን ንቃችሁ የወሰናችሁት ውሳኔ አሳዝኖናል። አጣሪ ኮሚቴ ለመላክ መወሰናችሁ ስህተት ነው አንልም ነገር ግን ማጣራቱን ሳትጀምሩ ገና ኑብረዕዱን ከቦታቸው ማንሳታችሁ ግን ትልቅ ስህተት ነው። እንዲህ ያለውን ፍርደ ገምድል ውሳኔ ለመቀበል የሚፈቅድ ልብ የለንም።” በማለት አጣሪ ኮሚቴውን አቀርቅሮ እንዲመለስ አድርገውታል።

Wednesday, November 7, 2012

ዓይነ መርፌው የጠፋበት ሲኖዶስና ሴራዎቹ

Ayne merfe
በዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል
እስራኤል በርካታ እግዚአብሔር የሚያስከፉ ከጠየቃቸው ጥያቄዎች መካከል ሳሙኤል በሸመገለ ጊዜ ንጉሥ ስጠን በማለት ያቀረቡት ጥያቄ ተጠቃሽ ነው። ይህን የእስራኤል አሳብና ጥያቄም እግዚአብሔር ክፉኛ እንዳሳዘነና ለጥያቄአቸውም በእስራኤል ሁሉ ላይ ንጉሥ ይሆን ዘንድ አህያ ፍለጋ የወጣውን የቢንያማዊው የቂስ ልጅ ሳዖል ንጉሥ አድርጎ እንደሰጣቸው በቅድሳት መጻህፍት በስፋት ታትቶ እናገኘዋለን። ንጉሥ ሳኦል በዋናነት የሚታወቀው ምንም እንኳን በእግዚአብሔር ፈቃድ የተሾመ ንጉሥ ቢሆንም እግዚአብሔር በመታዘዝ ባለመጽናቱ እግዚአብሔር የናቀው ከዚህ ጊዜ ጀምሮም ክፉ መንፈስ ያደረበትና መናፍስት ጥሪ ወደ ሆነች ሴት የሄደም ፍጻሜው ያላማረለት ታሪኩ ባነበብት ቁጥር ልብ  የሚሰብር ንጉሥ ነው። 
በእርግጥ የሲኖዶስ አመሰራረትና አነሳስ በተመለከተ በመጠኑም ቢሆን ከሐዋሪያት ሥራ መጽሐፍ ለመረዳት እንደሚቻለው ዓላማውና ግቡ የእግዚአብሔር ክብር ለመግለጥና እውነት የሆነችውን የጽድቅ መንግሥቱም በምድር ሁሉ  ላይ ለማስፋት እንደሆነ/እንደነበር ለመረዳት አያዳግትም። በሌላ መልኩ ያየነው እንደሆነም የአባቶች መሰባሰብና በህብረት መቀመጥ ጥቅሙ የሚያጠያይቅ አይሆንም።
ወደ ነባራዊው የራሳችን ጉዳይ የተመለስን እንደሆነ በአንፃሩ ነገሩ የተገላቢጦሽ ሆኖ ነው የምናገኘው። ሁላችን እንደምናውቀው ሲኖዶስ ተሰበሰበ በተባለ ቁጥር ለመስማት የምንጓጓው ዛሬስ በተራው ማን ይወገር ይሆን?፣ ማን ማንን ይዘልፍና ይዘነጥል ይሆን? የሚል ነው። እውነትም ስብሰባው በተጠናቀቀበት ቅጽበት ከወደ መገናኛ ብዙሐን በኩል የምንሰማውም "ለ … ያህል ቀናት ስብሰባውን ሲያካሂድ የሰነበተው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት ስብሰባውን አጠናቀቀ። ስብሰባው በርካታ ትእይንቶች የታየበት ሲሆን አቡነ እገሌ አቡነ እገሌ … ሲሉ መዝለፋቸውን፣ …  የውስጥ አዋቂ ምንጮችቻችን በደረሱን ዘጋባ ለማወቅ ተችለዋል"  ጨምሮ ሌሎች በርካታ የማይሰማ አሳዛኝ ነገር የለም።

Monday, November 5, 2012

የግብጽ ቤተክርስቲያን አቡነ ቴዎድሮስ ሁለተኛን 118ኛዋ ፓትርያርክ አድርጋ ሾመች


read in PDF:
ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎድሮስ አቡነ ቴዎድሮስ ሁለተኛ በመባል የግብጽ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን አዲሱ ፓትርያርክ ሆነው በትናንትናው ዕለት በመንፈስ ቅዱስ ተመረጡ፡፡ ለምርጫው የመጨረሻ እጩ ከነበሩት ከሁለቱ ሊቃነ ጳጳሳት እና ከአንድ መነኩሴ መሀል የመንፈስቅዱስን ሞገስ ያገኙት አቡነ ቴዎድሮስ ህዳር 9 ቀን በፓትርያርክነት ይቀባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ቤተክርስቲያኒቱ  በዕጣ ፓትርያርክ መሾም የጀመረችው በ18ኛው ክፍለ ዘመን ነው፡፡ የእግዚአብሐየር ፈቃድ ሆኖ ከ6 ዓመት ያልበለጠ ልጅ ዓይኑ በጨርቅ ታስሮ ባወጣው ዕጣ የተመረጡት አቡነ ቴዎድሮስ ሁለተኛ የ60 ዓመት አዛውንት ናቸው፡፡ እንደ አጋጣሚ ሆኖ የምርጫው ዕለት የልደታቸው ቀን የሆነው አቡኑ የሁኔታው መገጣጠም ብዙዎችን አስገርሟል፡፡

እ.ኤ.አ. በ1997 በጵጵስና የተቀቡት አቡነ ቴዎድሮስ ከካይሮ ዩኒቨርሲቲ የፋርማሲ ዲግሪ ያላቸው ሲሆን በመንፈሳዊ አባትነታቸው የተመሰገኑ እና የቤተክርስቲያኒቱ ቅዱስ ሲኖዶስም ሙሉ ድጋፍ ያላቸው አባት ናቸው፡፡

Friday, November 2, 2012

‹‹በጎውን ማን ያሳየናል የሚሉ ብዙ ናቸው››(መዝ. 4፥6)፡፡


Click here to read in PDF:Begowen
ስለ ዘመናችን ድንቅነት ብዙ ተነግሯል፡፡ የንግግሩ ምራቅ ሳይደርቅ ግን አሳዛኝነቱ ይተረካል፡፡ ዘመናችን ከተደነቀባቸው ነገሮች አንዱ የመረጃ ዘመን መሆኑ ነው፡፡ ሰዎች ስለ ራሳቸው ሳይሆን ስለ ሌሎች፣ ስለ ጎረቤታቸው ሳይሆን ስለ መካከለኛው ምሥራቅ ብዙ መረጃዎችን የሚሰሙበት ዘመን ነው፡፡ የመስማት አንዱ ዓላማ ለመመካከር፣ መራራው ወደ ጣፋጭ እንዲለወጥ ለመጸለይ ነው፡፡ የመረጃው ዘመን ግን ሰምቶ ማዳነቅ ብቻ ነው፡፡ ችግሮች ብዙ ናቸው፣ የመፍትሔ ድምፆች ግን አይሰሙም፡፡ ብዙ የመረጃ መረቦች የጭንቅ ወሬ ካጡ ይጨነቃሉ፡፡ የጦርነት፣ የተፈጥሮ አደጋ፣ የእርስ በርስ መተላለቅ ትልቅ ርእሳቸው ነው፡፡ 
በአገራችን በኢትዮጵያ በ1998 ዓ.ም መጀመሪያው ወር ላይ ከ1997 ጀምሮ በነበረው ግርግር አንድ የጋዜጣ አዘጋጅ ለጓደኛው ሲናገር፡- ‹‹ይህ ግርግር ሳይበርድ ለሦስት ወር ከቀጠለ የጀመርኩትን ቤት እጨርሳለሁ፡፡ አንድ ዓመት ቢቀጥል ምን የመሰለ መኪና ይኖረኛል፡፡›› እንዳለ፣ ጭንቅ ባላለቀ እያሉ የሚሳሉ፣ እንደ ዕድር ጡሩንባ ነፊ ሞተ እንጂ ተነሣ የማይሉ፣ እንደ ጠመንጃ አፈ - ሙዝ ከአፋቸው ደህና የማይወጣ፣ ያልተባረኩ አንደበቶች በዝተዋል፡፡ ብዙ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን እንለዋውጣለን፡፡ ሁሉም የሚያመነዥጉት ያንን ክፉ ነው፡፡ አዋቂዎቹ የሚሰጡት ትንታኔ የሚመጣውን ቀውስ ጠቋሚ ነው፡፡ ስለዚህ የግለሰቦች ቀውስ እያለፈ ዓለም ራሷ እየቀወሰች መሆኗን እንረዳለን፡፡ ግለሰቦች ሲቃወሱ ምድር ችላቸው ብዙ ዘመን ኖረናል፡፡ ምድር ከቀወሰች ግን ማን ይችላታል@