Wednesday, February 19, 2014

ቋሚ ሲኖዶሱ መጋቢ ሐዲስ በጋሻው አገልግሎቱን እንዲቀጥል ፈቀደ


በማህበረ ቅዱሳን ውል አልባ ክስ አገልግሎቱን አቋርጦ የነበረው መጋቤ ሐዲስ በጋሻው አገልግሎቱን እንዲቀጥል ተፈቀደ። ማኅበረ ቅዱሳን በአንካሳ ልቡ እያነከሰ ወንድሞችን ከቤተክርስቲያን ጠራርጎ የማስወጣት ዘመቻው አካል የሆነው የበጋሻው ክስ አቅሙ የሰለለ እና የምንፍቅናን ምንነት ያላገነዘበ መሆኑ ታውቆ አገልግሎቱ እንዲቀጥል መደረጉ ለእውነተኛ ኦርቶዶክሳውያን ሁሉ ትልቅ ድል ነው።
አሁንም ማኅበሩ ይህን እፍረቱን ተመለክቶ ወንድሞችን ማሰደዱን መክሰሱን ትቶ በእውነት ለቤተክርስቲያን የሚጠቅማትን ነገር ብቻ ላይ ቢያተኩር ይገባዋል እንላለን።
አሊያ የእውነተኛው ከሳሽ እና የሀሰት አባት የሆነው የዲያቢሎስ ደቀ መዝሙር እንደሆነ ይቀጥላል።