Thursday, January 23, 2014

ማኅበረ ቅዱሳን በአዲሱ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መዋቅራዊ ለውጥ ምክንያት እየደረሰበት ያለው ተቋሞ ተጋግሎ ቀጥሏል፡፡

REadin PDF:

በየሆቴሉ በድብቅ ይሰበሰባሉ ሲባሉ የቆዩት የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አለቆች በገሀድ በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ ተሰብስበው ፓትርያርኩንና አንዳንድ የማኅበሩን ደጋፊ ሊቃነ ጳጳሳት አስጠነቀቁ፡፡ ጥያቄዎቻችን ምላሽ የማያገኙ ከሆነ የቤተክርስቲያኒቱ አስተዳደር በጥቁር ራስ (መነኮሳት ባልሆኑ) ሰዎች እንዲካሄድ በሕጋዊ መልኩ እንደሚጠይቁ አስረድተዋል፡፡
የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት ሰራተኞች ቤተክርስቲያኒቱ የአሰራር ለውጥ እንደሚያስፈልጋት አምነው ለውጡ ሁለንተናዊና መላውን የቤተክህነቱ ክፍል ሊያቅፍ እንደሚገባ ሕጉም ከዋናው ከሕገ ቤተክርስቲያን መጀመር እንዳለበትና በየደረጃው ደንቦችና መመሪያዎች ሊወጡ እንደሚገባው አስረድተው ይህንን የሚሰራው አካልም ከቅዱስ ሲኖዶስ፣ ከሊቃውንት ጉባዔ፣ በየደረጃው ከሚገኙ የቤተክርስቲያኒቱ መዋቅር ሰራተኞች ፣ ከገለልተኛ ባለሙያዎች ምእመናንና የሰንበት ት/ቤት ተወካዮች በተወጣጣ ኮሚቴ መሰራት እንደሚገባው አስምረውበታል፡፡
ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ጥያቄያችሁ በቀላሉ የሚታይ አይደለም ትኩረት ይፈልጋል  በማለት ኮሚቴ እንዲቋቋም ፈቅደዋል በቤተክህነቱ አዳራሽ መሰብሰብ እንደሚችሉ አረጋግጠውላቸዋል፡፡
ስብሰባው ያበሳጫቸው አቡነ እስጢፋኖስ ግለቱ ከብዷቸው ወደ አሜሪካ እንደሚሄዱ ተናግረዋል፡፡

Friday, January 17, 2014

የአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በህዳር 12 ከተሰበሰበ ገንዘብ ከሁለት መቶ ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ተመዘበረ፡፡

በደብረምሕረት ቅዱስ ሚካኤል የደብሩ አስተዳዳሪ የዓመት ፍቃድ በመሆናቸው በቆጠራው ላይ ስላልተገኙ ይህንንም እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠርና የሰበካ ጉባዔ ምክትል ሊቀ መንበር ስልክ ተደውሎላቸው ቆጠራውን አቋርጠው በመውጣታቸው የደብሩ ዋና ጸሐፊ መ/ስ አብርሃም አቧይ  የወረዳው ስራ አስኪያጅ የአባ አእምሮ የቅርብ ዘመድ ከወረዳ የተወከሉት ወ/ሮ አባይ እና የሀገረ ስብከቱ ጸሐፊ ወ/ሮ አዲስ ዓለም እንዲሁም በአዲስ አበባ ሙስናና ዘረፋን በማበረታታት እነ የካ ሚካኤልን እንዳያገግሙ አድርጎ በዘረፋ ባዶ ያስቀራቸው በአዲስ አበባ ከተማ ለተለያዩ የውጪ ሀገር ኗሪዎች 7 ፎቅ ቤቶችን በተለያዩ አካባቢዎች  ሰርቶ የሚያከራየው ቀድሞ አለቃ የአደራው ንጉሤ ሴት ልጅ  ወ/ት እጸገነት አደራው በገንዘብ ያዥነት እንዲሁም በካቴድራሉ መልካም ሰው በመምሰል ለሁሉ ወዳጅ የሆነው አቶ ፋንታሁን ምረቴ እና ሊቀ ትጉሃን ኃ/ጊዮርጊስ በጋራ ዘረፋውን ማከናወናቸው ታውቋል፡፡