Monday, July 30, 2012

"ኢሳት"ና እውቀት ማዶ ለማዶ ተያዩ!

Esat andKnowledge:Click here to read in PDF
(ከጸሐፊው ግላዊ ገጸ መጽሐፍ(face book) የተገኘ)
በሙሉጌታ ወ/ገብርኤል
(ሐምሌ 23 2004 ዓ.ም.፣ ዐውደ ምሕረት/www.awdemihret.blogspot.com) (ባለፈው ሳምንት ኢሳት: በማቅ የአፍዝ አደንግዝ ፖለቲካ የተለከፈ የጽንፈኞች መናገሻ?” በሚል ርዕስ መቀመጫውን አምስተርዳም ያደረገ የዜና ማሰራጫ ማዕከል የሕዝብ ዓይንና ጆሮ፣ ሃብትና ንብረት መሆኑ እየቀረ ሕዝብንና ሀገርን ለመበታተን እንዲሁም ለማውደም ቆርጠው ከተነሱ የበግ ለምድ የለበሱ አደጋ ጣዮች ሥመ መንፈሳውያን በማበርና ድምጽ በመሆን በሰሚ ጆሮ ላይ እየፈጠርው ያለውን ሃላፊነት የጎደለበት ልቅ ውዥንብርና ብዥታ በመታቀብ ተቋሙ በዋናነት ለተቋቋመበትና ለተሰለፈበት ዓላማ ራሱን ያስገዛ ዘንድ በጥቂቱ ለማሳሰብ ያክል ተወያይተን ነበር በይደር የተለያየነው። ለዛሬ ታሪካዊ ስህተቶችን ብቻ በማተኮር ተፋለሶቹን አንድ በአንድ ነቅሰን አንጥረንና አበጥረን በሰፊው እንመለከታለን።
ጽሑፉ ምንም እንኳን "የዜጎች ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ታጋዮች" የሆኑ ድረ ገጾች በመላ የተላከ
ቢሆንም ድረ ገጾቹ በተላከላቸው ጽሑፍ ይዘት ምንም ዓይነት ተቃውሞ እንደሌላቸውና በጽሑፉ እውነትነት ቢስማሙም በይፋ ለማስነበብ ግን ፈቃደኞች ሳይሆኑ ቀርተዋል። በቋሚነት ሀገራዊ፣ ሃይማኖታዊና ማህበረሰባዊ አመለካከቴንና አስተሳሰቤን ከማካፍልበት ግዙፍ ኢትዮጵያዊ ድረ ገጽ ሕዝብ እንዳያነበውና እንዳያየውም ተቋሙ በፈጠረው ጫና 24 ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከስፍራው እንዲነቀል ተደርገዋል። ድርጊቱም - ዲሞክራሲያዊ በመሆኑ ሐዘን ተሰምቶኛል። በዚህ አጋጣሚ የዳያስፖራ "ነፃ ፕሬስ/ሚድያ" ነጻ ይውጣ! እያልኩ ለጊዜው ሥራዎቼን በመጽሐፈ ገጽ (face book) በኩል ለማስነበብ ተገድጃለሁ። ይህም እስኪታፈን ድረስ መሆኑ ነው እንግዲህ።
የጽሑፉ መልክ - ተንጋዶ የተጻፈውን ወይንም ደግሞ በኢታሊክ የሰፈረውን ከተናጋሪው ጋዜጠኛ ቃል
በቃል የሰፈረ ሲሆን መስመር የተሰመረባቸው ቃላት የእንግሊዝኛ ቋንቋ ቃላት ለመሆናቸው ለማስታወስ ነው።መልካም ንባብ!)

የጋዜጠኛው ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ስህተት÷
"ፋይናሊ ሊያሸንፉዋቸው ስላልቻሉ ምን ብለው ገቡ ክርስቲያኖቹን እኛም አመንን ብለው በቤተ-ክርስቲያን ውስጥ ገቡ። በሃይል ማሸነፍ ሲያቅታቸው ምን ውስጥ ገቡ ክርስቲያኖች ነን ብለው፤ ሳይሆኑ ክርስቲያን ነን ብለው ሃይማኖት ተቋምን መቆጣጠር ያዙ ከዛን ጊዜ ጀምሮ ነው የእምነት ተቋማት ቤተ-ክርስቲያን በገዢዎች ስር መዳፍ ስር እየወደቀችው ያለችውኢህአዴግ እያደረገው ያለው ከቄሳሮች የተለየ ነገር አይደለም በመስጊድም በቤተ-ክርስቲያን በኩልም ሁሉ ሊያደርግ የሚፈልገው እነዚህን ተቋማት ለእምነቱ ለእሱ ለአገዛዙ እንዲመቹት የማድረግ ነው:: ገብቶባቸዋል። በህገ መንግስቱ ላይ የነፃነቶች አለ ተብለዋል ኢህአዴግ ግን እንደፈለገ ገብቶ የራሱ አመራር አስቀምጠዋል
የኢሳት ጋዜጠኛ ደረጀ ሀብተ ወልድ

Thursday, July 26, 2012

ማህበረ ቅዱሳን እና የወደፊት እቅዱ

about mk: Read in PDF
(ሐምሌ 19 2004 ዓ.ም.፣ ዐውደ ምሕረት/www.awdemihret.blogspot.com) (ይህን ጽሁፍ ያገኘነው ፌስቡክ ላይ ነው። ጸሀፊው ራሱን ማህበሩ ውስጥ ሆነን የማህበሩን አደጋ ገልጠን የጠቆምን የቁርጥ ቀን የቤተክርስቲያን ልጆች” ሲል ይገልጻል። ጸሃፊው አለኝ በሚላቸው መረጃዎች መሰረት ጽሁፉን አዘጋጅቷል። የማኅበሩን የኑፋቄ ትምህርት ጨምሮ ጊዜ የምጠብቅላቸው ሌሎች መረጃዎች አሉኝ የሚለው ጸሐፊ እንደ ውስጥ አዋቂ የማኅበሩ እቅዶች እነዚህ ናቸው ሲል ይነግረናል። እንደ ጸሐፊው እምነት ማኅበሩ ከቤተክርስቲያን ተገንጥሎ እስከ መውጣት የጨከነ “ራዕይ” ያለው ነው። ለዚህም የሚረዳውን ጥናት የጨረሰ ሲሆን ተጨማሪ ጥናቶችን ለማድረግ ግብጽ ድረስ ሰው ልኳል ይለናል። በብሎጋችን እንዲወጡላችሁ የምትፈልጉዋቸው ጽኁፎች ካሉዋችሁ awdemihret@live.com ብላችሁ ብትልኩልን ይደርሰናል።  መልካም ንባብ)

ማህበረ ቅዱሳን ሁለት አይነት እቅድ አለው። አንደኛው ቤተክርስቲያኒቱን መቆጣጠር ሲሆን አሱ ካልተሳካ ደግሞ ሁለተኛውን ማለትም ሂደቶችን አይቶ በቂ የሚለውን አቅም ከገነባ በኃላ ወደፊት ተገንጥሎ የመውጣት ድብቅ ራዕይ አለው፡፡ ሁለተኛው አላማውም በቤተክርስቲያን ላይ አደጋ ለመፍጠርና አባላቱን ይዞ የራሱን ቤተ እምነት መመስረት ሲሆን ጉዞውን 40 በመቶ አድርሷል፡፡ ይህን እቅዱን ለማሳካት የተጠና እስትራቴጂ አዘጋጅቶ ተግባር ላይ አውሏል፡፡ ከእቅዶቹ ዋና ዋናዎቹ እንደሚከተሉት ይቀርባሉ

Tuesday, July 24, 2012

በአቡነ ጳውሎስ ስም የኤች አይ ቪ ኤድስ እና ቲቪ በሽታ ማገገሚያ ማዕከል ሊገነባ ነው

Abun pawlos center: Click Here To Read In PDF
  • “እግዚአብሔር ያዘዘን የማይለወጠው የማይሻሻለው ቃል ጠላቶቻችሁን ውደዱ የሚል ነው።”                                                                                         ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ
  • ማዕከሉ  በሁለት መቶ ሚሊየን ብር ይገነባል።

(ሐምሌ 17 2004 ዓ.ም.፣ ዐውደ ምሕረት/www.awdemihret.blogspot.com)በትናንትናው ዕለት በሸራተን አዲስ የአቡነ ጳውሎስን 20ኛ አመት በዓለ ሲመት አስመልክቶ በራእይ ለትውልድ በጎ አድራጎት ድርጅት  በተዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የኤች አይ ቪ ኤድስ እና ቲቪ በሽታ ማገገሚያ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ። 

ራዕይ ለትውልድ ባዘጋጀው በዚህ የእራት ግብዣ ላይ ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት ሚኒስትሮች ሌሎች ባለስልጣናት የጠቅላይ ቤተክህነት ሰራተኞች ባለሀብቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ ሰዎች የተገኙ ሲሆን የእለቱ የክብር እንግዳ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ነበሩ። ቅዱስነታቸው በቦታው ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከ10 ላይ በብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት ታጅበው የደረሱ ሲሆን እርሳቸው የክብር ቦታቸውን እንደያዙ መርሐ ግብሩ በራዕይ ለትውልድ ፕሬዝዳንት ብሌን ገነነ ንግግር ተከፍቷል። ወጣት ብሌን በንግግሯ ስለራዕይ ለትውልድ መጠነኛ መግለጫ የሰጠች ሲሆን ድርጅቱ በሴቶችና በሕጻናት ላይ እንደሚሰራና እና እስካሁን ድረስም እያደረገ ባለው አስተዋጽኦ ደስተኛ መሆንዋን ገልጻ እንዲህ ያለውን ዝግጅት ያዘጋጁበት ምክንያት ለሀገራቸውን እና ለህዝባቸው መልካም ስራ ሰርተው ላለፉ ኢትዮጵያዊያን መታሰቢያ እንዲሆን ታስቦ መሆኑን ግልጻለች። 

Sunday, July 22, 2012

ለማኅበረ ቅዱሳን ፍርሀት የሆነው ጉባኤ አርድዕት በጥሩ ሁኔታ እየተንቀሳቀሰ መሆኑ ታወቀ።

Gubae ardiet: Click Here To Read In PDF
  • ሊቀ ሥዩማን ኃይለ ጊዮርጊስ መኪና አልተቀማም
  • ጉባኤ አርድእት ስብሰባ እንዳይሰበሰብ አልታገደም
  • መንግስት ለማኅበረ ቅዱሳን የሰጠውን ማስጠንቀቂያ ማንም አልሰማም በማለት ወደ ጉባኤ አርድዕት ለማዞር ሞክረዋል
(ሐምሌ 15 2004 ዓ.ም.፣ ዐውደ ምሕረት/www.awdemihret.blogspot.com)የማኅበረ ቅዱሳን ብሎጎች በተለመደው ዋሾ ባህሪያቸው ያልሆነውን ሆነ እያሉ መዘገብን ቀጥለውበታል፡፡ ስለጉባኤ አርድዕት በመፈራረቅ በሰሩት ዜናም ገና በመደራጀት ላይ ያለውን ጉባኤ ተፈረካከሰ ተልፈሰፈሰ ሄደ ተመለሰ እያሉ የጅል ምኞታቸውን ይነግሩን ይዘዋል፡፡ ሊቀ ሥዩማን ሃይለጊዮርጊስም በጠቅላይ ቤተክህነቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ ፊርማ መኪናው ስለተበላሸ ቅያሪ መኪና እንዲሰጠው የትብብር ደብዳቤ እንደተፃፈለት እያወቁ  ደብዳቤውን ከኛ በቀር ማንም አያገኘውም በማለት ተበላሽቶ ወደ ጋራዥ የገባውን መኪና ተቀማ በማለት ዘግበዋል፡፡
እነዚህ የማኅበሩ የውሸት ቃል አቀባይ የሆኑ ደጀ ሰላምና አንድ አድርገን የተባሉት ብሎጎች በጉዳዩ ላይ እርስ በእርሳቸው እንኳ መስማማት አቅቷቸዋል። ዋሽቶ ስምምነት የት አለና?። ደጀ ሰላም ሀይለጊዮርጊስ መኪና የተቀማው በአቡነ ጳውሎስ ትዕዛዝ ነው ብላ ጀምራ ወደ ታች ወደ ወረድ ሲባል ደግሞ በምክትል ስራ አስኪያጁ በተስፋዬ ነው በማለት ራስዋን ተጣልታ ዘግባለች። አንድ አድርገን ደግሞ በምክትል ሥራ አስኪያጁ አቶ ተስፋዬ ነው ትላለች።
እውነታው ግን ሌላ ነው በምክትል ሥራ አስኪያጁ አቶ ተስፋዬ ፊርማ ተፈርሞ የወጣው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው የሃይለጊዮርጊስ መኪና በብልሽት መቆምዋን እና እንዲያውም ተለዋጭ መኪና እንዲፈለግለት ልማትና ክርስቲያናዊ መምሪያን የሚጠይቅ ነው።

Friday, July 20, 2012

የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ማኅበረ ቅዱሳን በስራዬ ጣልቃ እየገባ ስላስቸገረ አደብ ይያዝልኝ አለ

Addis abeba Hageresebket: Click Here to Read in PDF
(ሐምሌ 13 2004 ዓ.ም. ፣አውደ ምህረት/www.awdemihret.blogspot.com)ማኅበረ ቅዱሳን በማን አለብኝነት ወዋቅራዊ አሰራርን በመጣስ በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሥራ ላይ ጣልቃ በመግባት በስሩ የሚገኙ ገዳማትንና አድባራትን ሰበካ ጉባኤ ስብሰባ እየጠራ በቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠውን ከሶስተኛ ወገን የሚገናኝበትን መመሪያ እየጣሰ ይገኛል ሲል የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት አስታወቀ፡፡ 


ይህ የመዋቅር ጥሰት አግባብ ያልሆነ ስለሆነ ሃገረ ስብከቱ “…ማኅበሩ በሃገረ ስብከታችን ጣልቃ እየገባ የሚያስተላልፋቸውን ጥሪዎችና የመዋቅር ጥሰቶች እንዲያቆም…”የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት አካሄዱን የሚያተካክልበት መመሪያ እንዲሰጥልን እናሳስባለን ብሏል፡፡

Thursday, July 19, 2012

«ደጀሰላም» ብሎግ እንዴት እንደሚያጭበረብር ተመልከቱ!

(ደጀ ብርሃን ብሎግ ስለ ዳላሱ አቡነ አረጋዊ ቤተክርስቲያን ከዘገበች በኋላ መቀደሟ አበሳጭቷትና ከኔ የተረፈ ነው ለማለት ደጀ ሰላም ቀን አሳስታ ታሪኩን ለመዘገብ ሞክራለች፡፡ የማኅበረ ቅዱሳን የተንኮል ማቆሪያ ጣቢያ የሆነችው ደጀ ሰላም የምትተጋለትን የሐሰት ሥራዋን ምክንያታዊ ለማድረግ መሞከርዋ ለተፈጥሮዋ የሚስማማ ነው፡፡ ግን ጎግል ለማንም ስለማያደላ እና እንደ አንዳንድ ጳጳሳት ለማህበረ ቅዱሳን ስለማይሰራ የደጀ ሰላም የማጭበርበር ሙከራ ምን እንደሚመስል አሳይቶናል፡፡ ደጀ ሰላሞች ለምን አንዲህ እንዳደረጉ ደጀ ብርሃን በቂ ማብራሪያ ሰጥታበታለች፡፡መልካም ንባብ)
ምንጭ፡- ደጀ ብርሃን
        የማቅ አፈቀላጤ ስለሆነውና ከዳላሱ አቡነ አረጋዊ ቤተክርስቲያን ራሱን ስለገነጠለው ቄስ መሥፍን ማሞ አዲስ የሥራ ፈጠራ ጉዳይ በ10/11/2004 ወይም በ(17/7/2012) ዓ/ም  ዝርዝር ሀተታ ደጀብርሃን ብሎግ ማስነበቧ ይታወሳል። ከዚያም  ስለ ላስቬጋስ ኪዳነ ምሕረት ጢም አልባው መነኩሴ ጥቂት ዳሰሳ አድርገን ወደምእራቡ ክፍለ አሜሪካ ተጉዘን፤ በመምህር ወ/ሰማዕት ስለሚመራው ቅ/ሚካኤል ቤተክርስቲያን የማቅ ሰርጎ ገቦች እያደረሱ ስላለው የሁከት አገልግሎትና የረጋውን ወተት የመበጥበጥ ተልእኰ ከጠቃቀስን በኋላ የካሊፎርኒያና የዲሲ አካባቢ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ አባታዊ ጉብኝት ለማድረግ ወደ ሲያትል ደ/ም  ቅ/ አማኑኤል ቤተክርስቲያን  እንደሚያመሩ ዘግበን እንደነበር ይታወሳል።

አስቀድመን እንደዘገብነው የማቅ ሰርጎ ገብ በጥባጮች፤ በሀገር ቤቱ እንቅስቃሴ እየተዳከሙ ሲመጡ የውጪውን ሀገረ ስብከት የመጠብጠጥ እቅድ ነድፈው፤ የቆየ  ዐመላቸውን እየተገበሩ ይገኛሉ። በቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ጉብኝት ያደርጋሉን የሰማው መምህረ ሁከት ማቅ አንድም ቀን ተኝቶላቸው እንደማያውቀው ሁሉ አስቀድሞ ጆሮውን አቅንቶ የብጥብጥ አጁን በመዘርጋት እንቅፋት መፍጠሩን ቅንጣት ሳያፍር «ደጀ ሰላም» የተባለው የማቅ ማእከላዊ ኰሚቴ ቃል አቀባይ ብሎግ  ዘግቦ አስነብቦናል።  ወደ ሁከትና ዐመጻ እንዲገቡ የሚቀሰቅሳቸውና የስህተት መንገድን አሰማምሮ ስለቅድስና እንደመታገል አድርጎ በኅሊናቸው በመሳል የሚያነሳሳቸው ከሌለ በስተቀር ምእመናን የዋሃን ናቸው። ገንዘባቸውን፤ ጉልበታቸውንና እውቀታቸውን ለአገልግሎት የሚያበረክቱትን እነዚህን የዋሃን የእግዚአብሔር ቤተሰቦችን ማቅ እንዴት መጠምዘዝና ለተፈለገው ዓላማ ማዋል እንደሚቻል ብዙ የሥራ ልምድ ስላለው ይህንኑ ጥበበ ዐመፃውን በሲያትል አማኑኤል ቤተክርስቲያን  ተግባራዊ አድርጎ ብጹእ አቡነ ፋኑኤልን የመቃወም ህውከት ለመፍጠር ሞክሯል። 

Wednesday, July 18, 2012

መንግስት ለማኅበረ ቅዱሳን የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጠ

masetenqeqiya lemk: Clicl HEre to Read in PDF
(ሐምሌ 11 2004 ዓ.ም. ፣አውደ ምህረት/www.awdemihret.blogspot.com)የበቀለውን እየነቀለ የታጨደውን እየበተነ ቤተክርስቲያንን የሁከት መንደር ያደረገው ማኅበረ ቅዱሳን አሰራሩን እንዲያስተካክል የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ተሰጠው።
ማስጠንቀቂያው የተሰጠው በሐምሌ ወር መጀመሪያ ላይ ሲሆን የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች  የማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች ጠርተው ውስጣቸውን እንዲያጠሩ፣ ሃይማኖቱ ከሚፈቅድላችሁ ወሰን ወጥተው ከሚፈጽሙት ድርጊት እንዲቆጠቡ፣ ከየትኛውም የአመጽ ሥራ በስተጀርባ ጥላቸውን እያጠሉ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ እንዲገቱ፣ ከሌላ ጽንፈኛ ሐይል ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያቆሙ፣ ቤተክርሰቲያኒቱን በመበጥበጥና ስራዋን ሁሉ እቆጣጠራለሁ በማለት የሚያደርጉትን ሩጫ እንዲገቱ አካሄዳቸውን የማያስተካክሉ ከሆነ ግንከዚህ በላይ ሊታገሳቸው እንደማይችል እና መንግስት የሰበሰባቸው መረጃዎች ማኅበሩን ለማፍረስ እና በወንጀልም ለመጠየቅ በቂ  እንደሆኑ ተነግሯቸዋል።
ከአመሰራረቱ ጀምሮ እጁን በደም ነክሮ የተነሳው ማኅበር በተለያዩ ወንጀሎች እየተጠላለፈ አሁን ያለበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ እነ እሸቱ ለዛር እያደነከሩ የ8 ሴቶች ክብረ ንጽህናን ገፈው የመሰረቱት ማኅበር በደም አበላ እየተነከረ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ሲፈጽማቸው የነበሩ የነብስ ግድያ የሙስና እና የተለያዩ ወንጀሎች በሙላት የሚታወቁ ሲሆን ያስጀመራቸው የዛር መንፈስ የደም ግብሩን በየአመቱ በተለያየ መንገድ እየተቀበለ ይገኛል፡፡ 

Tuesday, July 17, 2012

የዳላሱ አቡነ አረጋዊ የማቅ ወኪል ቄስ ከግንድ ላይ ተገንጥሎ በኪራይ ቤት ውስጥ ተተከለ!

Dalas : Click here to read in PDF
ምንጭ ደጀ ብርሃን
(እራሱን በሚመለከት ሥርዓተ ቤተክርስቲያን መጣስ ስህተት የማይመስለው፣ እውነትን ለሲዖል አውራሽ ራዕዩ የሰዋው አሸባሪው ማኅበረ ቅዱሳን ባልበላው አንኳ ጭሬ ልድፋው በሚለው አስተምሕሮው የአሜሪካኑን ሓገረ ስብከት እየበጠበጠ ይገኛል፡፡ መንፋሰዊ አገልግሎት ምንነት ያልገባቸውን አባ ኤውስጣጤዎስን ይዞ የመበጥበጥ ሥራውን ይፋዊ ያደረገው ማኅበር ተረት ሰፈር ተወልዶ ተረት ሰፈር ያደገውን ሊቀ ተረታት ወድርቅናታት የሰውን ስራ ገልብጦ በማሳተም ጉዳዮችተመራማሪ የሆነውን ወይ ጸጋ አሊያም የንግግር ውበት የሌለው እና እንጨት ነክሶ የሚጮኸውን ዳንአል ክብረት አዝማች አድርጎ ሶስተኛ ሲኖዶስ ለማቋቋም እየጣረ ይገኛል፡፡ 

ዳንኤል በሀገር ቤቱ ማቅ ፊት ስለነሳው የአሜሪካውን ማው ሙጥኝ ካለ ሰነባብቷል፡፡ ሁከት እንጂ ሰላም በማይስማማው መንፈሱም አሜሪካንን ለመበጥበጥ ታጥቆ ተነስቷል፡፡ ማቅ የአገር ሰው ሢሞቅ በማንኪያ ሲቀዘቅዝ በእጅ እንደሚለው ሀሳቡ በሚፈጠምበት ቦታ ላይ የሀገር ውስጥ ሲኖዶሱ የኔ ነው እያለ ሀሳቡ ከልካይ ባጣበት ቦታ ላይ ደግሞ ከሀገር ውስጥ ሲኖዶስ ውጭ ነኝ በማለት መበጥበጡ ይህ ማህበር እውነት ባይኖረው ይሉኝታ የለውም ወይ ያሰኛል? ዳላስ ከተማ ላይ ማኅበሩ እየሰራው የሚገኘውን ስራ በዝርዝር የሚያስነብብ ዘገባ ደጀ ብርሃን ሰርታለች፡፡ መልካም ንባብ ይሁንላችሁ፡፡)
በመሠረቱ ቤተክርስቲያንን ለመንፈሳዊ አገልግሎት ማቋቋም ቀና ሃሳብ መሆኑ አይካድም። ጥፋት የሚሆነው አንዲቱን ቤተክርስቲያን ለማዳከምና ምእመናን በቡድን ለመከፋፈል ሲባል ከሆነ የመንፈሳዊ ተግባርን እሳቤ በማደብዘዝ ስውር ዓላማን ለመፈጸም መንፈሳዊ ካባን የደረቡ ወረበሎች የሚጠቀሙበት ስልት መሆኑ እየታየ ነው። እናም ቄስ መሥፍን የተባለው የዳላስ አቡነ አረጋዊ ቤተክርስቲያን ሰባኬ ወንጌል የነበረው ግለሰብእ የተሰጠውን የማቅን ተልእኰ አንግቦ በኅቡእ የቆየ ቢሆንም ሰዓቱ ሲደርስ ከዛሬ ጀምሮ ተገንጥያለሁ ማለቱ ተሰምቷል።
በኢትዮጵያ ሀገር ውስጥ  ያለ ዋና ሲኖዶስ ፤ በስደት ያለ ዋና ሲኖዶስ እና  አሁን ደግሞ በፓትርያርክ ማኅበረ ቅዱሳን የሚመራ አዲስ ሲኖዶስ በምድረ አሜሪካ እየተገነጠለና ራሱን እያራባ ወደ ሦስትነት እያደገ ይገኛል።
በዳላስ አቡነ አረጋዊ ወተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን ሰባኬ ወንጌል የሆነው የማኅበረ ቅዱሳኑ ታማኝ ሎሌ ለመገንጠልና በይፋ አውጆ በ5000 ዶላር ቤት ተከራይቶ የወጣ ሲሆን  መነሻ ምክንያት  የሆነው ነገር ሲቃኝ እንዲህ መሆኑን ምንጮቻን አረጋግጠዋል።

Monday, July 16, 2012

ሐረርና አዲሱ የዘረኝነት ምጧ

Harerena zeregenete :Click here to read in PDF
ወንድም ነኝ ከሐረር

(ሐምሌ 9 2004 ዓ.ም. ፣አውደ ምህረት/www.awdemihret.blogspot.com)በዘመናት ሀሉ መካከል ዘረኝነት ዘረኝነት ቋሚ የኢትዮጵያ ችግር ሆኖ ቀጥሏል። እንደ ንጉሱ አጎንብሱ በሚባልበት የፖለቲካው አለም ያለው ዘረኝነት ምንጩ የኔ ዘር ለምን ከስልጣን ወረደ የገሌ ዘር እንዶት አገር ይመራል ከነገስኩ ዘሬን ላንግስ ከሚሉ ስጋዊ ምክንያቶች የሚመነጭ ነው። ፖለቲካው ከስህተቱ እየተማረ ነገሮችን ማስተካከል የሚችልበት እድሉን ለመጠቀም አያመነታም። እንደ ኢትዮጵያ ባለ ሀገር ዘረኝነት የትም እንደማያደርስ ሲረዳ ዘረኝነትን በታማኝነት ተክቶ ለፖለቲካው ሲስተም ታማኝ ኦከሆኑ ድረስ ከየትኛውም ብሔር የተገኘውን ሰው ይጠቀማል። ፖለቲካ ዘረኝነትን ቢያስብ ትክክል ነው ባይባልም አይደንቅም። ፖለቲካ የአለም ስርዓት ነው ዘረኝነትም አለማዊነት ነው።
ዘረኝነት አገሬ በሰማይ ነው ብላ ልታምን በሚገባት በቤተክርስቲያን ሲከሰት ግን ኃዘናችን ከፍ ይላል። ዛሬ ዛሬ ከተወሰኑ አገልጋዮች በቀር ከጳጳስ እስከ ዲያቆን ሀገሩ በሰማይ ሳይሆን ወይ በትግራይ ወይ በጎንደር አሊያም በጎጃም… ነው። የእግዚአብሔርን ሥራ በእግዚአብሔር ቃል ሳይሆን በብሔራቸው መነጽርነት የሚመዝኑ አገልጋዮች ለቤተክርስቲያኒቱ ፈተና ሆነውባታል። የብሔራቸው ሰው በዙሪያቸው እስከተከማቸ ድረስ የትኛውንም የእግዚአብሔር ቃልና ሓሳብ ለመጋፋት ወደ ኋላ አይሉም። 

Saturday, July 14, 2012

በበርካታ መጽሐፍቶቹ የሚታወቀው የዲያቆን አሸናፊ መኮንን ጉዳይ አነጋጋሪነቱ እንደቀጠለ ነው።


 D/n Ashenafi case: Click here to read in PDF
ዺ/ን አሸናፊ በሲኖዶሱ ስብሰባ ወቅት ግንቦት 9 ያስገባው ደብዳቤ
የሰኔ 25 የዲያቆን አሸናፊ አቤቱታ
(ሐምሌ 7 2004 ዓ.ም. ፣አውደ ምህረት/www.awdemihret.blogspot.com) “…የምንሠራው ሥራ ከሌላ ሥራ ሊኖር እንደማይችል ሁሉ የምንኖርለት ዓላማ ከሌለም ትክክለኛ ሕልውና ሊኖር አይችልም፡፡ በርግጥ ሰዎች የሚኖሩለት ነገር ሁሉ ዓላማ ተብሎ ሊጠራ አይችልም፡፡ ዋነኛ ዓላማው እግዚአብሔርን ማወቅና መከተል ነው፡፡ ሌሎች ዓላማዎች ሁሉ ከትልቁ ዓላማ ውስጥ የሚወጡ ናቸው፡፡
አንድ ሰው የሰው ዋጋው ስንት ነው? ብሎ ከጠየቀ በኋላ የሰውን ዋጋ ለማወቅ እግዚአብሔርን ጠይቁት ብሏል፡፡ አንድ ዕቃ የራሱን ዓላማና ዋጋ ማስረዳት አይችልም፡፡ የዕቃው ዝርዝር ዓላማና ዋጋ ያለው ራሱ ጋ ሳይሆን ሠሪው ጋ ነው፡፡ ስለዚህ የዕቃውን ዓላማና ዋጋ ለማወቅ ሠሪውን መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ አዎ የሰው ልጅ ለትልቅ ዓላማ የተፈጠረ ፍጡር ነው፡፡ ይህንንም ሊያሳውቀን የሚችል እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡
 ሕይወት ግባችንን ትጠይቀናለች፡፡ መድረሻችንን ካላወቀች በነጻነት አትለቀንም፡፡ እግዚአብሔር በዓላማ ፈጥሮናል፡፡ በአጋጣሚ ወይም በስህተት አልተፈጠርንም፡፡ የተፈጠርንበት ዓላማም እኛ ዓላማ ከምንለው ከመውለድ መክበድ ያለፈ ነገር ነው፡፡ የክርስትናው ጉልህ ነጥብ እግዚአብሔርን መቀበልና ራስን መቀበል ነው፡፡ ብዙዎች ራሳቸውን ሳይቀበሉ እግዚአብሔርን ተቀብለናል ይላሉ፡፡ ከዚህ ነገር የተነሳም በክርስትናቸው ደስታ የላቸውም፡፡ ባለዓላማ የሚያደርገን እግዚአብሔርንና ራሳችንን መቀበል ነው፡፡
እግዚአብሔርን ስንቀበል የምናገኘው የመጀመሪያው ጸጋ ራሳችንን መቀበል ነው፡፡ ቀለማችንን፣ ዘራችንን፣ ቋንቋችንን፣ ቤተሰባችንን፣ ማንነታችንን እንቀበለዋለን፡፡ እግዚአብሔር የሰጠን ማንነት መለወጥ የማንችለው መለኮታዊ ምርጫ ነው፡፡ በዓለም ላይ እኛን የምንመስል እኛ ብቻ ነን፡፡ እግዚአብሔር ግልባጭ የሌለን ኦርጂናል አድርጎ ፈጥሮናል፡፡ በመልካችን፣ በአመለካከታችን፣ በተሰጦአችን፣ በትከሻችን፣ በአረማመዳችን፣ በድምፃችን፣ በአሻራችን፣... ልዩ ነን፡፡ ፊትን በምታህል ትንሽ ገጽ  ስድስት ቢሊየን ሕዝብ የተለያየ መልክ ተስሎበታል፡፡ ይህ የሰው ሥራ ቢሆን አንዱ ሰው ስንት ጊዜ በተደገመ ነበር፡፡ 

Friday, July 13, 2012

“ኢሳት”: በማቅ የአፍዝ አደንግዝ ፖለቲካ የተለከፈ የጽንፈኞች መናገሻ!

esat :Click here to read in PDF
በዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል

(ሐምሌ 6 2004 ዓ.ም. ፣አውደ ምህረት/www.awdemihret.blogspot.com)(ይህ ጽሑፍ የተወሰደው / ሙሉጌታ ወልደገብርኤል ለረጅም ጊዜያት ፖለቲካዊ፣ ሃይማኖታዊና ማህበረሰባዊ አመለካከታቸውን በቋሚነት ከሚገልጹበትና ከሚጽፉበት ታዋቂ ከሆነው "ከኢትዮጵያ ሪቪውድረ ገጽ ሲሆን በአሁን ሰዓት ግን ጽሑፉ ከስፍሯው ተነስቷል። መልካም ንባብ )
 
አሁን አሁን “ኢሳቶች ምን ነው ያለጸባያቸው?” ተብሎ ዜናዎቹ፣ ዘገባዎቹና ሐተታዎቹ በቸልተኝነት የማለፉ ነገር ወደ መሟጠጡ ተደርሷል።[1] ጉልህ የአደባባይ ሞያዊ ህጸጾቹንና ሥነ- ምግባራዊ ችግሮቹንም በፈቃደኝነት ለመነጋገርና በመተማመን ላይ የተመሰረተ የእርምት እርምጃ ለመውሰድ ራሱን ካላዘጋጀና ችግሮቹንም ለመፍታትም ዝግጁ ካልሆነ ማዕከሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን በተመልከተ ለሚሰራቸው ዜናዎች፣ ለሚያቀርባቸው ዘገባዎችና እንዲሁም ቁንጽል ሐተታዎች የሄደበትን ርቀት ያክል በመጓዝ ከስር ከስር ተገቢ ምላሽ መሰጠቱ የማይቀር ነው።
ይህም በመሆኑ ችግር ያለበት ችግር ፈጣሪ ወከበኛ ካልሆነ በስተቀር እውነትን በማድበስበስና በማዳፈን በአንጻሩ ነጭ ሐሰትንና ቅጥፈትን በመዝራት፣ ውዥንበርም በመፍጠር ለጥቂት ግለሰቦናችና ልሂቃን የሥልጣን ጥም ማርኪያ ተብሎ በሕዝብ ደካማ ጎን በመግባት ንጹሐን ዜጎች በኃይማኖት ስም በመቀስቀስም አላስፈላጊ መስዋዕት እንዲከፍሉ የማድረጉ የ“ማህበረ ቅዱሳን” የመተላለቂያ ስልት መኆን መቀበል የማይቻል ነገር ነው፡

Thursday, July 12, 2012

አቡነ አብርሃም ከሐረር ሰንበት ተማሪዎች ተቃውሞ ገጠማቸው።

aba abreham tqawemo harer: Click here to read in PDF
(ሐምሌ 5 2004 ዓ.ም. ፣አውደ ምህረት/www.awdemihret.blogspot.com) ቤተክርስቲያን የሁሉም ልጆችዋ ነች። አባትም ሁሉን እንዲወድ ሁሉን እንዲጠብቅና ሁሉን እንዲመራ የሰማይ ትእዛዝ አለበት። ወገንተኝነት አባታዊ ባኅሪ አይደለም። ለሚሻለው ለወደዱት ታጥፎ ሰግዶ የጠሉትን ደግሞ አይንህን አያሳየኝ ማለት እንኳን ለጳጳስ ለአንድ የቀበሌ ሹምም ተገቢ ጸባይ አይደለም። ሸክሙን ማን እንደሰጠ ማስተዋል ከተቻለ ትከሻን አስፍቶ መጠበቅ ይገባል። በስማ  በለውና አንድን ወገን ለማስደሰት ተብሎ የሚሰራም ስራ ኋላ ላይ ማጣፊያ እንደሚያጥር ግልጽ ነው።
 ለማኅበረ ቅዱሳን ካደሩ የሰነበቱት አቡነ አብርሃም ሀረር ከተማ ውስጥ ያሉትን የሰንበት ተማሪ ተወካዮች ሰብስበው “የካሴት መዝሙሮችን ማዳመጥና መዘመር አቁማችሁ የማኅበረ ቅዱሳንን መዝሙሮች እየገዛችሁ ስሙ በጉባኤም አነርሱን ዘምሩ።” ብለው ለማዘዝ በመሞከራቸው ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል። 

Wednesday, July 11, 2012

ቤተክርስቲያንህን እወቅ የሚለው መጽሐፍ የማኅበረ ቅዱሳን የመጽሐፍ ምንተፋ (plagiarism) ውጤት ነው።

Teru minche Vs Betekerestiyanihene eweke. Read in PDF
ማኅበረ ቅዱሳን ከሚታወቅበት የክፋት ሥራዎቹ መካከል አንዱ የሰውን ጽሑፍ በመስረቅ እና የራሡ ሀሳብና እቅድ አድርጐ በሚያሳትማቸው መጽሔቶቹ፣ ጋዜጦቹ መጽሐፍቶቹ ላይ በማውጣት ነው፡፡ አንባቢ ከኔ ወዲህ ላሳር ብሎ የሚያምነው ይህ ማኅበር አይታወቅብኝም ብሎ የሰው ሥራ እየመነተፈ ከሳተማቸው መጽሐፍት መሀል ለዛሬ አንዱን እናያለን።
ይህ ሊቅ የማያስወድድ ባህሪው እያንደረደረ እና እያንቀዠቀዠ ወስዶ ይወገዙልኝ ካላቸው በርካታ ግለሠቦች መካከል የሀገራችንን የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ እድገት እዚህ ደረጃ ያደረሡ፣ 42 የሚደርሡ መጽሐፍቶችን የዳሰሱ ይልቁንም እንደነ ጎህ-ጽባሕ እና አዲስ ዓለም የተሠኙ መጻሕፍቶችን የደረሱ እና ባለ ትልቅ ራዕዩና ከዘመናቸው ቀድመው የተፈጠሩት ታላቅ ሰው ይጠቀሳሉ። እኚህ ታላቅ ኢትዮጵያዊና ኦርቶዶክሳዊ (በማ.ቅ. አጠራር ፕሮቴስታንታዊ ተሀድሶ ተብለው የተፈረጁ) ክቡር ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ ይባላሉ፡፡ እኚህ ታላቅ አባት ከነ ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ ከነ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ከነ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም እና ከነ ፕሮፌስር ጌታቸው ኃይሌ ጋር ፕሮቴስታንታዊ ተሀድሶ ተብለው የተፈረጁ ሲሆን ማኅበሩ ይህን  ስም የሰጣቸው ስራዎቻቸውን ሁሉ ካስወገዘ በኃላ በስሙ ለማሳተም ፈልጎ ነው ወይ የሚል ጥያቄ ያስነሳል።

Tuesday, July 10, 2012

በጽንፈኝነትና በአክራሪነት መንፈስ የሚራገቡ የአደባባይ ተረታ ተረቶች የታሪክ ሐቅን ሲገዳደሩ፡- በኢትዮጵያ ታሪክ «አልነጃሺ» የተባለ የሰለመ ንጉሥ ነበርን. . .??

                            (ከሪፖርተር ጋዜጣ የእሁድ ሐምሌ 1/2004ዓ.ም እትም ላይ የተወሰደ)
ጸሐፊው፡- ፍቅር ለይኩን፡፡ nejasi. click here to read in PDF
ከጥቂት ወራት በፊት የመንግሥታቸውን የሥራ ሂደት ሪፖርት ለማሰማትና ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት በፓርላማ የተገኙት ክቡር ጠቅላይ ሚ/ር መለስ ዜናዊ በሀገራችን ከጊዜ ወደ ጊዜ መስመሩን እየሳተ እየሄደ ስላለውና አንዳንድ በሃይማኖት ሽፋን የአክራሪነትና የጽንፈኝነት እንቅስቃሴን ስለሚያራምዱ ግለሰቦችና ቡድኖች ባስተላለፉት ማስጠንቀቂያና ማሳሰቢያ በሚመስል ንግግራቸው፡- ‹‹እንዲህ ዓይነቱን በሃይማኖት ሽፋን እየተካሄደ ያለውን ማንኛውንም ዓይነት የሀገርን ሰላምና ጸጥታ የሚያደፈርስ የአክራሪነትንና የጽንፈኝነትን እንቅስቃሴ መንግሥት ችላ እንደማይለውና በንቃት በመከታተል እርምጃ እንደሚወስድም በግልጽ አስረድተው ነበር፡፡››
ጠቅላይ ሚ/ሩ አክለውም በሀገራችን ኢትዮጵያ ለዘመናት ታሪካዊና ጥንታዊ የሆኑት ሁለቱ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና ለረጅም ዘመናት በሀገራችን ተከባብረውና ተዋደው የኖሩና ይህ ልዩ የታሪክ እውነትም የተቀረው ዓለም እስከ አሁንም ድረስ የሚደነቅበትና በመልካም አርዓያነቱ የሚጠቅሰው መሆኑን አስታውሰው ይህን እውነታ የሚያስረግጥ አንድ ገጠመኛቸውን ለፓርላማው አባላት እንዲህ አቅርበው ነበር ጠቅላይ ሚ/ር መለስ ዜናዊ፡-
በቅርቡ አሉ ጠቅላይ ሚ/ሩ አንድ ከወሎ ክ/ሀገር የገጠር ቀበሌ የመጣ ሰው/ወደጃቸው በዛ ቀበሌ ዝናብ በመጥፋቱ ምክንያት ድርቅ ስላጠቃቸው በቀበሌው ያሉ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኝ ክርስቲያኖች ታቦታቸውን ነቅለው ወደ ሌላ ቦታ ለመሄድ መቁረጣቸውን የሰሙ የእስልምና እምነት ተከታዮችና የዕድሜ ባለጸጋ አባቶች ክርስቲያን ወገኖቻቸውን ይህ ታቦት የእናንተ ብቻ እኮ አይደለም የሁላችንም ነው፡፡ በዚህ ቦታ ለብዙ ዘመን ቆይቷል እናም እባካችሁ ከዚህ ቦታ አትንቀሉት እኛም አላህን እንለማመናለን እናንተም እግዜርን ተማጠኑ በማለት ክርስቲያኖቹ ታቦታቸውን ነቅለው እንዳይሄዱ እንዳገላገሉ ለፓርላማው አባላት ተናገረው ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚ/ሩ በዚህ ንግግራቸው ሊያስተላልፉ የፈለጉት መልእክት ለብዙዎቻችን ግልጽ ይመስለኛል፡፡ በታሪካችን የቆየውና እንደ ምሳሌ የምንጠቀስበት በሃይማኖቶች መካከል ያለው መከባበርና መቻቻል በዚህ ዘመን በአንዳንድ በሃይማኖት ሽፋን ጽንፈኝነትና አክራሪነትን በሚያራምዱ ግለሰቦችና ቡድኖች እንዴት እየደበዘዘ፣ እየጠፋና መስመር እየለቀቀ እንዳለ ያሳሰቡበት መልእክት ይመስለኛል፡፡

Sunday, July 8, 2012

የጉጂ ቦረና ሐገረ ስብከት ችግር መንስዔው እና አሁን ያለበት ሁኔታ

gugi borena: Click here to read in PDF
የጉጂ ቦረና ሊባን ዞኖች ሀገረ ስብከት በማኅበረ ቅዱሳን አማካኝነት የተቀሰቀሰው ችግር እስካሁን አልተፈታም። ችግሩ አሁንም የማኅበሩ አባልና የቁርጥ ቀን ልጅ በሆነው ሲያምር ተ/ማርያም በተባለ ግለሰብ መሪነት በማኅበሩ ጭፍሮች አቀናባሪነት እየሄደ ያለበት መንገድ የህዝቡን ትዕግስት ያስጨረሰ ሲሆን ከብዙ የገንዘብ ጉድለቶች ጋር ተያይዞ ስሙ የሚነሳው ይህ ግለሰብ አሁንም በቦታው ተመልሼ ካልተመደብኩ በማለት ችግር እየፈጠረ ይገኛል።
ችግሩ ሲቀሰቀስ መነሻ የሆነው ዋነኛ ጉዳይ ሁሉን ልምራ ሁሉን ልቆጣጠር የሚለው ማኅበረ ቅዱሳንን የወቅቱ የጉጂ ቦረናና ሊበን ዞኖች ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሳዊሮስ በኔ ሀገረ ስብከት ይህን ማድረግ አትችልም አቅምህን አውቀህ ኑር ብለው በማዘዛቸው ነው። በወቅቱ ይህንን ለማስፈጸም የሚያስችል አቅም ስላልነበረው ውስጥ ውስጡን አድፍጦ ከቆየ በኋላ አቡነ ሳዊሮስ አካባቢውን ለቀው ወደ ወሊሶ ከመጡ በኋላ ማኅበሩ የአመጽ ስራውን በግላጭ ጀመረ።
ችግሩ የተጠነሰሰው የአካባቢው ባለ ሀብቶች ለሻኪሾ ማርያም ቤተክርስቲያንን መንበር እኛ እናሰራ በማለት ጥያቄ ባቀረቡ ጊዜ ማን ይስራው የሚል ጥያቄ በተነሳበት ወቅት ነው። የአካባቢው ባለሀብቶችና የቤተክርስቲያንዋ ሰበካ ጉባኤዎች ጨረታ ወጥቶ ይሰራ ሲሉ እነ ሲያምር ደግሞ ማኅበረ ቅዱሳን ይስራው በሚል ይሞግታሉ። ይህ ነገር እየከረረ ሄዶ መጨረሻ ላይ በጨረታ ይሰራ የሚል ውሳኔ ላይ ሲደረስ እነ ሲያምርም ነገሩን የተቀበሉ በመምሰል ጨረታው እንዲወጣ ታዞ የረጅም ጊዜ ልምድ ያላቸው መጋቢ ጥበባት ጸጋ ዘአብ አሸነፉ። መጋቢ ጥበባት ጸጋ ዘአብ በመንበር ሥራ ታዋቂ ግለሰብ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡  የገንዘብ ነገር የማይሆንለት ማቅም በዚህ ነግር ጥርሱን ነክሶ አቡነ ሳዊሮስን ለመዋጋት ተነሳ። ህዝብ ሁሉ ሰለሚደግፋቸው ግን አቡነ ሳዊሮስ በቦታው ላይ እያሉ ምንም ማድረግ አልቻሉም፡፡ ሲያምርም በሁሉ ነገር ታዛዣ መስሎ በውስጡ ግን ነገር እየበላ ከማኅበሩ ጋር እየሰራ ቆየ፡፡ አቡነ ሳዊሮስም ከፍተኛ የሳይነስ ህመም ስላለባቸው በግንቦት 2002 ሲኖዶስ ዝውውር እንዲደረግላቸው ጠየቁ፡፡ 

Thursday, July 5, 2012

የ"ማኅበረ ቅዱሳን" የሰሞኑ የገጽታ ማሻሻያ (Facelift) ሙከራ

getseta mukera: Click her to read in PDF
ምንጭ፡-ደጀ ሰላም(dejeselaam.blogspot.com)
ሰሞኑን (ሰኔ 25 ቀን 2004 .) የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን "አንድ ሀገር አንድ ሃይማኖት" በሚል ርዕስ ዶኩሜንታሪ ፊልም አቅርቦ ነበር፡፡ በዚህ ፊልም ኢቴቪ ሊያስጨብጥ የፈለገው እውነት በኢትዮጵያ ውስጥ የሃይማኖቶች መቻቻል ጥንት የነበረና ያለ፣ ለወደፊቱም መቀጠል ያለበት መሆኑን ነው፡፡ በዚሁ ዘገባው አንዳንድ ሃይማኖቶችንና ተቋማቸውን የማይወክሉ የጽንፈኝነት አዝማሚያዎች በየጊዜው መታየታቸውን በማሳየት አፍራሽ ጎናቸውን ለማንጸባረቅ ሞክሯል፡፡ መልዕክቱ ከሞላ ጎደል የተዋጣለትና ጥሩ አቀራረብ ነበረው፡፡
አስተያየታችን ያነጣጠረው ስለዘገባው ይዘትና በሃይማኖቶች መካከል ስላለው መቻቻልና የጽንፈኝነት አዝማሚያዎች ለመተቸት ሳይሆን፣ አንዳንድ በየመንግሥት ተቋሙ የሚገኙ "ማኅበረ ቅዱሳን" አባላት ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ለማኅበራቸው ገጽታ ግንባታና ማኅበሩ ለሚያደርሰው የጥቃት ሽፋን ለመስጠት ምን ያል እንደሚፍጨረጨሩ ለማሳየት ነው፡፡