Saturday, June 30, 2012

የቅድስት ሥላሴ መንፋሳዊ ኮሌጅ ዲን ተመራቂ ተማሪዎችን ማደሪያ ከለከሉ፡፡

Click here to read in PDF
በቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ዲን ከመመደባቸው በፊት ተማሪዎች ግቢውን መልቀቅ የለባቸውም የሚለውን መመሪያ ጥሰው ተማሪዎቹን ከግቢ አስወጡ፡፡ መነኮሳትን ጨምሮ አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ማደሪያ አጥተው እየተንከራተቱ ይገኛሉ፡፡ እስከአሁን ደረስ ባለው ሕግ መሰረት ተመራቂ ተማሪዎች ምደባ እስኪደረግላቸው ድረስ በኮሌጁ ውስጥ ማደር መብታቸው ነበር።ተማሪዎቹ ችግራቸውን ለቅዱስ ፓትርያርኩ ያስረዱ መሆናቸው ሲታወቅ እሳቸውም የኮሌጁ የበላይ ጠባቂ እንደመሆናቸው በቤታችሁ ማደር መብታችሁ ነው፡፡ መመሪያውን ማፍረስም አይቻልም ስለዚህ ሂዱ እቤታችሁ እደሩ ብለው ቢያዙም የኮሌጁ ዲን ግን ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡

Friday, June 29, 2012

የፍቅር ለይኩን አላማ ማኅበረ ቅዱሳንን መታደግ ወይስ እውነትን መዋጋት

Click here to read in PDF
ፍቅር ለይኩንን በግሌ በጣም አደንቀዋለሁ። በማንኛውም ርዕስ ጽሁፍ ሲጽፍ ነገሮችን በሚያይበት ዕይታ በእጅጉ እመሰጣለሁ። አገር ውስጥ ያሉ መጽሔቶች ለምን አምድ እንደማይሰጡት ሁሌም ግራ ይገባኛል። አገሩን እና ቤተክርስቲያንን የሚወድበትን ፍቅር ያንንም የሚገልጽበትን መንገድም አደንቃለሁ። ነገር ግን ማኅበረ ቅዱሳን ጋር ሲደርስ ሚዛናዊነቱን ሚዛን ያሳጠበት ምክንያት እየደነቀኝ ግን መልስ ልሰጠው ተገድጃለሁ። በመጀመሪያ አባ ሰላማ ላይ በጻፈው ጽኁፍ ካለኝ ከበሬታ አንጻር በዝምታ ላልፈው ብፈልግም ለደጀ ብርሃን የሰጠው የመልስ መልስ ግን ያለመናገር መብቴን ስለገፈፈው በጽኁፉ ላይ ያሉትን ሚዛን ያጣባቸውን ነገሮች ለመተቸት ተገድጃለሁ።
ላለፉት ስድስት አመታት አቡነ ጳውሎስ በዘረኝበት በሌብነት በተሃድሶነት ተጠርጥረው ሲሰደቡ አቡነ ገሪማ አቡነ ፋኑኤል አቡነ ሳዊሮስ ያለስማቸው ስም እየተሰጣቸው ሲሰደቡ ዲያቆን አሰግድ በሀሰት በከፍተኛ ደረጃ ስሙ ሲጠፋ ወንጌል ሰበክ ተብሎ ፓስተር ሲባል መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ለምን እውነትን አገለገልክ ተብሎ በከፍተኛ ደረጃ የስነ ምግባር ጉድለት በተቀነባበረ ካሴት ካደ ሲባል አባ ሰረቀብርሃን በህጋዊ መንገድ ሂዱ ባሉ በጠላትነት ተፈርጀው ሲብጠለጠሉ እነ አእመረ፣ ሀይለጊዮርጊስ፣ ኑብረዕድ ኤልያስ፣ ዲያቆን ትዝታው፣ መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል፣ በሪሁን፣ ተረፈ፣ ያሬድ፣ ታሪኩ……በተለያዩ የማኅበረ ቅዱሳን ብሎጎች በከፍተኛ ደረጃ ሲብጠለጠሉ እንደ ተራራ የተቆለለው ትዕግስትህ ምነው አውደ ምህረትና አባ ሰላማ በጻፉት ጽሁፍ ጊዜ እንደ ገለባ ክምር ተበታተነ?

Thursday, June 28, 2012

የሊቀ ስዩማን ኃይለ ጊዮርጊስ ሹመት ለመላው ሰሜን አሜሪካ አህጉረ ስብከት የስቴት ቤተክህነቶች ተላለፈ

Click here to read in PDF
ሰሞኑን ጉባኤ አርድዕትን ለማቋቋም እየሰራ ነው በሚል የማኅበረ ቅዱሳን የነገር በኩር ብሎግ ደጀ ሰላም ከፍተኛ የስም ማጥፋት ውንጀላ ያደረገችበት ሊቀ ስዩማን ኃይለ ጊዮርጊስ የመላው አሜሪካ አኅጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅነት ሹመት ለመላው የሰሜን አሜሪካ አህጉረ  ስብከት ተላለፈ። በመንፈሰ ጠንካራነቱ እና ቤተክርስቲያንን በቅንነት ለማገልግል ባለው ተነሳሽነትና ጥረት የሚታወቀው ሊቀስዩማን በተሰጠው ሹመት ተገቢውንና ቤተክርስቲያንን የሚጠቅም ስራ ይሰራበታል ተብሎ ይታመናል።
ኃይለጊየርጊስ በተሾመበት ሥልጣን ላይ የነበሩት በቅርቡ የክብር ክህነቱ የተሻረው ዶክተር መስፍንን ጨምሮ በሙሉ የማቅ አባላት ሲሆኑ አቡነ አብርሃም ለማኅበሩ ያላቸውን ታማኝነት ያረጋገጡበት ሹመት እንደነበር ይታወቃል። እነ ክህነት በጉልበቱ መስፍንም የስራ ድርሻቸው እስኪጠፋቸው ድረስ የእውር ድንብር መውተርተራቸው ያስከተለው ችግር ይስተካከል ዘንድ እንደ ሊቀ ስዩማን ኃይለ ጊዮርጊድ ያሉ ሰዎች መሾማቸው ተገቢ ነው።
ሊቀ ስዩማን ኃይለጊዮርጊስ እስከአሁን ድረስ በቤተክርስቲያን ውስጥ እያደረገ ያለውን አስተዋጽኦ የሚያውቁ ሰዎች በአህጉረ ስብከቱ የተለየና ጠንካራ ስራ የመስራት አቅሙን በአግባቡ የሚያሳይበት ዕድል አግኝቷል ይላሉ። 

Wednesday, June 27, 2012

ቆሞስ አባ ሠረቀ ብርሃን ወልደ ሳሙኤል ከቀረበባቸው የስም ማጥፋት ክስ ነጻ መሆናቸውን ቅዱስ ሲኖዶስ ገለጸ!


ምንጭ፤ የሰንበት /ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ድረ ገጽ

መምህር አባ ሠረቀ ብርሃን ወልደ ሳሙኤል (ቆሞስ) ከሳሹ በአግባቡ በማይታወቅ መልኩ የቀረበባቸውን የስም ማጥፋት ክስ በጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ስለቀረበ ቅዱስ ሲኖዶስም በወቅቱ የክሱን እውነተኝነት ለማጣራት ኮሚቴ እንዲቋቋም መወሰኑ ይታወቃል።

የዔደን ገነቱ እባብ “ማኅበረ ቅዱሳን”

click here to read in PDF
(ይህ ጽኁፍ አራት ኪሎ አካባቢ ሲበተን የተገኘ ሲሆን ማኅበረ ቅዱሳንን በተመለከተ እየተዘጋጀ ያለ ተከታታይ ጽሁፍ ዘጠነኛው ክፍል ነው። ከዚህ ጽሁፍ በፊት ያሉትን ጽሁፎችን ለማግኘት ሙከራ አድርገን የነበረ ቢሆንም የጽሁፉን አዘጋጅ ማወቅ ስለአልተቻለ ጽሁፎቹ አልተገኙም። በዚህ ጽሁፍ የማኅበረ ቅዱሳንን ምስረታ አስመልክቶ እስካሁን ድረስ ከሰማናቸው ሀሳቦች ለየት ያለሀሳብ ይዞ የቀረበ ነው። ማኅበረ  ቅዱሳን ከእውነተኛ የቤተክርስቲያን ልጆች ጋር መግባባት ሲገባው እኔ ያልኩትን ተቀበል አሊያ አንተም አትኖርም በሚል ደካማ አስተሳሰብ የቤተክርስቲያን ልጆች እያሸማቀቀ ያለ ሲሆን ስጋ እንጂ መንፈስ  የሌለበት መሆኑም ታውቋል። የማኅበሩ ኃሳብ አላማና አካሄድ ከአመሰራረቱና ከስም አወጣጡ ጀምሮ ፖለቲካዊ ይዘት ያለው መሆኑን የሚያስረዳው ይህ ጽኁፍ አቡነ ገብርኤል የማኅበሩን ስም ማኅበረ ቅዱሳን ያሉበትን ምክንያት የዋህ አባላቱና ሌሎች ሰዎች ከሚያስቡት እጅግ በተለየ መንገድ ያቀርባል። ማህበረ ቅዱሳን እንደ ኤደን ገነቱ እባብ ስቶ የሚያስት ወድቆ የሚጎትት ታውሮ ልምራ የሚል መሆኑን የሚያውቁ ሁሉ የኤደን ገነት እባብ መባሉን ተገቢነት ይስማማሉ። መልካም ንባብ) 

1.    የማኅበሩ ህቡዕ የፓለቲካ አደረጃጀት ከመሠረቱ ሲታይ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሐይማኖታዊ ስምና ግብር ራሱን ሰውሮ የሚገኘው ሐይማኖታዊ ፈቃድ የያዘ ግን ደግሞ ያልተመዘገበ የፖለቲካ ፓርቲ ሆኖ የሚንቀሳቀሰው “ማኀበረ ቅዱሳን” ከጅማሬው በደርግ ዘመን በ1982 ዓ.ም በብላቴ አየር ወለድ ማሰልጠኛ ካምፕ ገብተው ከሰለጠኑ በኋላ ጋምቤላ መተከልና ፓዌ ዘምተው የነበሩት ወታደሮች ኋላም በዝዋይ ሃመረ ኖህ ላይ የተጠለሉት ሰዎች ተሰባስበው የመሰረቱት የወታደሮች ፓርቲ (“ማህበር”) ነው፡፡
ፊታውራሪ አመዴ ለማ የሕይወት ታሪካቸውን ባሳተሙበት መጽሐፍ ውስጥ ገጽ 217 ላይ በኤርትራ ውስጥ የጣሊያንንና የእግሊዞችን ቅኝ ግዛት ተቋውሞውን በሽምቅ ውጊያ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆኖ ዓላማውን ሲያራምድ የነበረ “ማኅበረ ቅዱሳን” የሚባል ህቡዕ ድርጅት እንደነበረና የድርጅቱ መሪ ደጃዝማች ሐረጎት አባይ እንደነበሩና በቅርበት እንደሚያውቁትም አመዴ ለማ ጠቁመዋል፡፡

Tuesday, June 26, 2012

የደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ቤተክርስቲያን የሰራተኛ ጉባኤ የተመሰረተበትን አራተኛ አመት በድምቀት አከበረ።

click here to read in PDF
የደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ቤተክርስቲያን የሰራተኛ ጉባኤ የተመሰረተበትን አራተኛ አመት በኩክ የለሽ ማርያም ቤተክርስቲያን ባለፈው እሁድ አከበረ። ወደ ኩክ የለሽ ማርያም በተደረገው ጉዞ ምዕመናኑ የተለያዩ ዝማሬዎችን እየዘመሩ  የተጓዙ ሲሆን ለተጓዡ ህዝብ ደስታና በረከት የሚሆንም የእግዚአብሔር ቃል በጉዞው ወቅት ተሰብኳል። በዓሉ የሰራተኛ ጉባኤው ሲመሰረት ጀምሮ የነበሩ አገልጋዮችን ያካተተ ሲሆን በጉዞው ላይ ከነበሩት አገልጋዮች መካከልም ማክሰኞ ማክሰኞ ለረጅም ጊዜ ያገለገለው መጋቢ ሀዲስ በጋሻው ጉባኤው ሲጀመር ለረጅም ጊዜ ተከታታይ ትምህርት የሰጠው  መምህር አሰግድ ሳህሉ የደብሩ ሰባኪያነ ወንጌል መምህር ታሪኩ አበራ እና መምህር ናሁሰናይ መላከ ሰላም አስቻለው መሀሪ የደብሩ ካህናት እና ሌሎችም ሲሆኑ ከዘማሪያንም ዲ/ን ዕዝራ ኃ/ሚካኤልና ዲ/ን ታምራት ሃይሌ ተገኝተዋል።
ወደ ኩክ የለሽ ማርያም ጉዞ ለማድረግ 60 ሰው የሚጭኑ 12 መኪናዎችን ተዘጋጅተው የነበረ ሲሆን የተዘጋጁት መኪናዎች እነዚህ ብቻ በመሆናቸውም በርካታ ሰዎች አብረው መጓዝ እየፈለጉ መጓዝ ሳይችሉ ቀርተዋል። ሌሎች ሰዎችም መኪኖቹ መሙላታቸውን ሲያረጋግጡ የራሳቸውን አማራጭ በመውሰድ በቤት መኪናና በትናናሽ ሚኒባሶች ጉዞውን የተቀላቀሉ ሲሆን የቤት መኪኖቹና የሚኒባሶቹ ብዛት ምዕመኑ ላመነበት ነገር ምን ያህል ዋጋ ለመክፈል የተዘጋጀ መሆኑን ያሳየ ነበር።
ኩክ የለሽ ማርያም እንደደረሱም ጉዞው በደብሩ አስተዳደር ሸኒ ደብዳቤ ዕውቅናን ያገኘ ስለነበር ተጓዡ ህዝብ ኩክ የለሽ ማርያም በነበሩ ማኅበረ ካህናት መልካም አቀባበል ተደርጎለታል። በቤተክርስቲያንዋ ዓውደ ምሕረት መምህር አሰግድ ያስተማረ ሲሆን በመምህሩ ላይ ያደረ የእግዚአብሔር መንፈስ ምዕመኑን በከፍተኛ ደረጃ አጽናንቷል። 

Monday, June 25, 2012

የማኅበረ ቅዱሳን መሠሪ መገለጫዎች

Click here to read in PDF
ምንጭ፡- ደጀ ብርሃን
አንዳንዶች ማኅበረ ቅዱሳንን የሕይወታቸው አንድ አካል አድርገው ይመለከቱታል። የማኅበረ ቅዱሳን ሞት ሞታቸው፤ ሕይወቱ ደግሞ ሕይወታቸው አድርገው ስለሚመለከቱ ሲወቀሱ ወይም ሲተቹ ኅሊና እንዳለው ሰው ሳይሆን ዛር እንደሰፈረበት ሰው ያንዘፈዝፋቸዋል፤ ያወራጫቸዋል። እስከለሞት  ስለሚሟገቱለት ማኅበር፤ ማንነት ተረጋግተው አሳማኝና ማስረጃ ያለው መልስ በመስጠት  በግንዛቤ የተሳሳተ ካለ በመመለስ ወይም እንደጠላት የሚቆጥሩትን ክፍል የሚንቁ ከሆነም ዝም ብለው እንደትቢያ ቆጥረው  ከማለፍ ይልቅ ስድብ፤ ዛቻና ማስፈራሪያ፤ ጴንጤ፤ ተሐድሶ፤ መናፍቅ፤ አህያ፤ ውሻ፤ ደደብ፤ ከሐዲ፤ ሌባ  ወዘተ ቃላቶችን በመጠቀም ተቀናቃኝ ነው ለሚሉቱ ሁሉ መጠቀምን ባህላቸውና የእምነታቸው አንዱ ክፍል በማድረግ ሲጠቀሙበት መመልከት እንግዳ ነገር አይደለም። ከአፍቃሬ ማኅበሩም ይሁን የማኅበሩ አንድ አካል ከሆኑት አባላቶቹ የሚሰጡን አስተያየቶች የሚያሳዩን  ያንን ነውና።
ከዚህ ሁሉ አስተሳሰቦቻቸው የምንረዳው ነገር ቢኖር የማኅበረ ቅዱሳን አባላትም ይሁኑ የደጋፊዎቹን  ማንነት ሲሆን  ከእነሱ የተለየ ሃሳብ ላለው ሁሉ መልስ መስጠት የማይችሉ፤ ነገሮችን ሁሉ በኃይልና በዘለፋ ለመፍታት የሚመኙ፤ «ሁሉም መንገዶች ወደ ማኅበረ ቅዱሳን ያመራሉ» ካልሆነ በስተቀር ሌላ መስማት የማይፈልጉ ስታሊናዊ አመለካከት የታጠቁ ሰዎች ስብስብ መሆናቸውን  ብቻ ነው።
አሁንም ስለማኅበረ ቅዱሳን መሠሪ ማንነት የምናቀርባቸውን አንዳንድ ነጥቦችን ተከትለው ያንኑ የተለመደ አፋቸውን በመክፈት ከዚያ አልፎ ያለውን የአእምሮአቸውን በር ከፍተው  እንደሚያሳዩን በመጠበቅ፤ የማኅበሩን መሠሪነት የሚጠቁሙ ጭብጦችን በአስረጂ ለማስቀመጥ እንሞክራለን።

የሰለፊያው ማኅበር ማኅበረ ቅዱሳን በቤተክርስቲያን ሊቃውንት ላይ ያሴረው ሴራ ተጋለጠ!!

Click here to read in PDF
በከላይነው ትዕዛዙ
ሰሞኑን ጉባኤ አርድዕት የሚባል ማኅበር ተቋቋመ ከሚለው ዜና ከተሰማ ጀምሮ ማኅበሯ ከፍተኛ ስጋት ላይ ወድቃለች። ከዚህም የተነሳ ይህን ማኅበር አቋቁመዋል እና የማህበሩ ደጋፊ የመሆን ዕድል አላቸው የሚሉትን ሰው ሁሉ ከጠቅላይ ቤተክህነት የስልጣን መዋቅር ለማንሳት ቆርጠው ተነስዋል።
ለዚህም የተከተሉት እስትራቴጂ ለማኅበሯ ድጋፍ የሚሰጡ የቤተክህነት ሰራተኞችን ተጠቅሞ ዝውውር ማድረግና ሊፈጠር ይችላል ብለው የሚጠረጥሩትን አንድነት ማላላት ነው። ለዚህም ይረዳቸው ዘንድ የማኅበሩ ሰዎች በአሁኑ ሰዓት ብዙ ጊዜያቶችን የሚያጠፉት በእስክንድር ገብረክርስቶስና የጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ በሆነው በአቶ ተስፋዬ ውብሸት ቢሮ ውስጥ እንደሆነ የቤተክህነት ምንጮች ይገልጻሉ፡፡ ተስፋዬ ጠንቃቃና ከማኅበሩ ጋር ያለው ግንኙነት እንዲታወቅበት የማይፈልግ ሰው ሲሆን አስክንድር ግን ባለው ከፍተኛ የንዋይ ፍቅር ለማኅበሩ ያለ ይሉኝታ ሙሉ በሙሉ መገዛት የጀመረ ሰው ነው።
ማኅበሩ ከመታው ድንጋጤ ለመረጋጋትና ከገባበትም ማጥ ለመውጣት የተለያዩ ሥልቶችን  እያውጠነጠነ ቢሆንም ብዙዎቹ ዘዴዎቹ ፈር ሊይዙለት አልቻለም፡፡ በአሁኑ ሰዓት በጠቅላይ ቤተክህነት እየታየ ያለውን ነገር ስንመለከት ማኅበሯ ከከበባት ዘርፈ ብዙ ችግሮች ነጻ ለመውጣት ካሳባቸው አማራጮች አንዱ መሆኑን እንረዳለን። ጤናማ አእምሮ ሊያስብ የሚገባውን ነገር ከማሰብ ይልቅ የተለያዩ ተንኮሎችንን የስም ማጥፋት ዘመቻዎችን በሽብር ብሎጎቹ እየከፈተ የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን ገና ለገና ጠንካራ ማኅበር ተቋቁሞ ቤተክርስቲያኒቱን ለብቻችን የማስተዳደር ፍላጎታችንን ይጋፋብናል። እየተቆጣጠርነው የመጣነውን የቤተክሀነቱን አስተዳደር ከቁጥትራችን ውጭ ያደርግብናል። በሚል ከወዲሁ በጉባኤ አርድዕትና በመስራች አባላቱ ላይ ከፍተኛ የስም ማጥፋት ዘመቻ ከፍቷል። 

Saturday, June 23, 2012

አባ አብርሃም ኢየሱስ አያዋጣም አሉ!!

Click here to read in PDF
በሀረር ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ለሦስት ቀናት የቆየ እጅግ ደማቅ መንፈሳዊ ጉባዔ ተካሂዶ ነበር። በወንጌል ወዳድነቱ የሚታወቀው የሐረር ህዝብ በሶስቱ ቀን ጉባዔ በከፍተኛ ሁኔታ የተገኘ ሲሆን በጉባኤው ሰዓት የክልሉ ሊቀ ጳጳስ የሆኑት አባ አብርሃም አገልጋዮቹን ጠርተው “…ይሔ ኢየሱስ ኢየሱስ የምትሉት የሚያዋጣችሁ  አይመስለኝም። ብትተዉት ይሻላል።” በማለት ተናገሩ።
የአባ አብርሃም የጉድ ሙዳይ በከፈቱት ቁጥር በውስጡ የተደበቀ ነገር እየወጣበት ከማስደነቅ አልፎ ማሳዘን ከማዛዘንም አልፎ ማስደንገጥ ጀምሯል። ይህ ንግግራቸው ሰውየው በቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ያላቸው አጀንዳ ምንድን ነው? አሰኝቷል። ህሊናቸውን ተጠቅመው የሚያደርጉት ነገር እንደሌለ እና ማኅበረ ቅዱሳን ከሰጣቸው ተልዕኮ ውጭም ሌላ አጀንዳ እንደማይታያቸው ያሳየው እንዲህ ያለው ንግግራቸው ከወንጌሉ እውነት ውጭ መስማት በማይፈልገው የሐረር ሕዝብ ፊት እንዲፈጸም በማዘዛቸው ትዕዛዛቸው ሳይሳካለት ቀርቷል። ከዛም በኃላ ደግሞ የደብሩን አስተዳዳሪ ጠርተው “…ይሄ ኢየሱስ ኢየሱስ የምትሉትን የማያዋጣ ጉዞ መቸ ነው የምትተዉት?...” ሲሉ ለመውቀስ ሞክረዋል። 

Friday, June 22, 2012

ትግሉ በሕዝብና በ"ማኅበረ ቅዱሳን" መካከል ነው፤ ቤተክርስቲያን ለአደጋ ተጋልጣለች ቢሆንም በመጨረሻው ሙሽራው እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ አሸናፊ ነው

Click here to read in PDF
ምንጭ፡-http://dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com

"ማኅበረ ቅዱሳን" "እውን የማኅበረ ቅዱሳንና ኦርቶዶክስ 'ተሐድሶ' ፍልሚያ ወይስ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሕልውና ጉዳይ"? በሚል ርዕስ  ደጀ ሠላም (deje selam) በተባለው ትዊተር ገጹ ላወጣው የማደናገሪያ ጽሑፍ የተሰጠ መልስ

ድሮ ልጆች ከሚያውቁት ሠፈር ርቀው እንዳይሄዱና እንዳይጠፉ ጭራቅ ይበላሃል፤ ጭራቅ ይበላሻል እየተባሉ በዐዋቂዎች ማስፈራሪያ ይደረግባቸው ነበር፡፡ ይህ ጭራቅ በሕይወት የሌለና በምናብ የተፈጠረ ሲሆን፣ ጥርሶቹ ሾል ሾል ያሉ፣ ሁለት ትልልቅ ዓይኖች ከፊት፣ ሁለት ትልልቅ ዐይኖች ደግሞ ከማጅራቱ /ጭንቅላቱ/ በኩል በድምሩ አራት ዐይኖች ያሉት ሲሆን አንገቱን ዞር ዞር ማድረግ ሳያስፈልገው በሁሉም አቅጣጫ ስለሚመለከት ማንም ሊያመልጠው አይችልም፡፡

ጭራቅ በቁመናው ሰው እየመሰለ ከሰው መካከል በተለይ ልጆችን እየመረጠ፣ ወስዶ በትልቅ ጋን ውስጥ እንዳለ በመክተት ከቀቀለ በኋላ ያለ ቢላዋ ሥጋቸውን የሚነጭ አውሬ ነው ይባል ነበር፡፡ ምንም እንኳን ጭራቅ በግዑዙ ዓለም የሌለና የፈጠራ መሆኑን ብናውቅም በአባቶችና በእናቶች በተደረገብን ጫና ሳቢያ ዛሬም ያለ የሚመስለን ሰዎች ቁጥር ቀላል አይደለም፡፡

አባቶችና እናቶች ልጆችን እንዲታዘዙ የሚያደርጉት በጭራቅ በማስፈራራት ነበር፡፡ እኛም ልጆች በጊዜው ጭራቅ መጥቶ እንዳይበላን የተሰጠንን ሥራ ባንወደውም ሠርተናል፡፡ ጀንበር ሳይጠልቅ ወደ ቤት ስብስብ ብለን እግራችንን ታጥበን፣ እራት በልተን ተኝተናል፡፡ አፋችን ክፉ ቃል እንዳያወጣ ገደብ ተደርጎበታል፡፡ ጭራቅ እንዳይበላን አባትና እናታችን ጉያ ውስጥ ውሽቅ ብለን፣ ፍርሃት እንደናጠን አድገናል፤ ኖረናል፡፡

Thursday, June 21, 2012

የማኅበረ ቅዱሳን አመራር አባላት ማኅበሩን እየለቀቁ ነው፡፡

Click Here to Read in PDF
ከይሔ ነው እውነቱ
ሲመሰረት የነበረውን ውጫዊ አላማ አድንቀው እና ወደው ቤተክርስቲያኒቱን በተደራጀና በተጠና መንገድ ለማገልገል የፈለጉ አንዳንድ የዩኒቨርስቲ ምሩቃንና “በጎ” ዓላማውን የደገፉ ግለሰቦች ማኅበሩን ቀረብ ብለው ሲያዩት እና ውስጣዊ አላማውን ሲረዱ እንደ ድቡልቡል አለት ተገትሮ ለመጨበጥ የማይቻል መሆኑን በመረዳታቸው ተራ በተራ እየለቀቁት መሆኑ ተሰማ። እነዚሁ ከአባልነት እስከ ከፍተኛ አመራር ሰጪነት የደረሱ የስራ አመራር አባላት ለማህበሩ የወገብ ትጥቅ ሆነውለት በከፍተኛ ደረጃ ሌሎች  አባላት የሚመኩባቸው የነበሩ ቢሆንም ለራሳቸው በገባቸው የማህበሩ ከፋፋይ አጀንዳ ዕጣ ለእነርሱም ወጥቶ ሊሰሩ የፈለጉትን ሥራ በአግባቡ ለመስራት ባለመቻላቸው ምክንያት ማኅበሩን ለመልቀቅ ወስነው የመልቀቂያ ደብዳቤ አስገብተዋል።
በእግዚአብሔር ሀሳብ ቀዳሚ የሆነውን አህዛብን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ እያጠመቃችሁ ደቀ መዛሙርት  አድርጉአቸው የሚለውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ተልዕኮ ቸል ብሎ ወንጭፍ ወርዋሪ አገልግሎት ላይ ራሱን የጠመደው ማኅበረ ቅዱሳን ራሱን ጠልፎ የሚጥል እንቅስቃሴ ከጀመረ ሰንብቷል። ከቤተክርስቲያን የአገልግሎት ራዕይ መቀበል ሲገባቸው ያልሰከነ ስሜታቸውን አጀንዳ በማድረግ ግለሰብ ተኮር እንቅስቃሴ በማድረግ ደግመው እንኳን ሊያጣሩት የማይፈልጉትን ጥርቅምቃሞ ወሬ ማስረጃ ብለው በመያዝ እንደ አበደ ውሻ እየተክለፈለፉ ያሉት የማህበሩ ሰዎች ውድቀታቸውን በሚያፋጥን እንቅስቃሴ መጠመዳቸው እያስተዛዘበ ይገኛል። በዚህ ግለሰብ ተኮር እንቅስቃሴ ከየት እንደሚነፍስ የማይታወቅ ነፋስ አባላቱን ተረጋግተው የተሰበሰቡለትን ዓላማ ተፈጻሚ እንዳያደርጉ አጀንዳ በመስጠት ከቤተክርስቲያኒቱ አባቶችና ከፖለቲካው ጋር እያላተማቸው ነው፡፡ በዚህ ግጭት መካከል የራሳቸውን አጀንዳ የሚያስፈጽሙ ጆቢራዎች ግን በሌላው ቁስል ኑሮቸውን እያስተካከሉ አላማቸውን እያስፈጸሙ ይገኛሉ፡፡

Wednesday, June 20, 2012

ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎቹን አስመረቀ

Click here to read in PDF
  • መምህር አሰግድ ሳሕሉም ከተመራቂዎቹ አንዱ ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በስሯ ከምታስተዳድራቸው መንፈሳዊ ኮሌጆች መካከል አንዱና የ69 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ የሆነው አንጋፋው ቅድስት ሥላሴ ኮሌጅ ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በተገኙበት አስመረቀ። የምረቃ ፕሮግራሙ ደማቅ የነበረ ሲሆን ተማሪዎቹ ቤተክርስቲያንን በቅንንነትና በመልካም ሥነ ምግባር ለማገልገል ቃል ገብተዋል። አዳራሹ በተመራቂዎችና በቤተሰቦቻቸው የተሞላ የነበረ ሲሆን በእያንዳንዱ ተማሪ ፊትም የሚታየው ደስታ ስሜት ልዩ ነበር። በዕለቱ አባታዊ ቡራኬ የሰጡት  ቅዱስ ፓትርያርኩም  “…ያለፉትን ዘመናት መሰናክሎችን እያለፍን መምጣታችን ስለምናውቅ ያለፉትንም ያለፍነው በራሳችን ስላልሆነ አሻጋሪውን አምላክ ከሁሉ በፊት እናመሰግናለን። እናንተ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በኃላፊነት ላይ ነው ያላችሁት እያስረከብናችሁ ነው። በዚህ የተመደበ ሌላ ሥራ የለውም የወንጌል ሥራ በትርፍ ጊዜ የሚሰራ አይደለም። ሁሉንም የምንማረው በጊዜ ነው። ከዚህ በፊት ተምረው የወጡ ብዙ ናቸው። በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ያሉ የገቡትን ኪዳን ይፈጽሙ አይፈጽሙ ተመልካቹ አምላክ ነው። መለኮታዊ አደራ ስለሆነ።….” በማለት አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አክለውም “…ከየትም ተነስቶ ለሃይማኖት ጠበቃ መሆን አይቻልም። ለሃይማኖት ጠበቃ ለመሆን ከእንደዚህ ካሉ መንፈሳዊ ኮሌጆች ተምሮ መውጣት ያስፈልጋል። በምድር ላይ ብዙ እውቀት ብዙ ትምህርት አለ። ያን እናከብራለን። ከየትም ተነስቶ ሃይማኖታዊ ነገር ለማድረግ አይቻልም። መንፈሳዊ እውቀት ከእንደዚህ አይነት ኮሌጆች ነው የሚወጣው።...
ከእንግዲህ በኃላ የዶግማችን የሥርዓታችን የቀኖናችን ምስክሮች አስተማሪዎች እናንተ ናችሁ። የሚጠበቅብን ትውልድ ማሳረፍ ነው። ከመንፈሳዊው ትምህርት ውጪ በሆነ እውቀት ፍልስፍናና ትምህርት የተራቀቀ ለእኛ ሃይማኖታዊውን እውነት የሚያብራራልን ሰው የለም። ከቤተክርስቲያናችን ሥርዓት ጋር አብሮ መታሰብ ያለበት አገልግሎታችንን የፍቅርና የሰላም ማድረግ ነው። በትዕዛዝ እኛ ያልናችሁን ፈጽሙ የሚል ግዳጅ አይሰራም።

Tuesday, June 19, 2012

እጃችሁን ለእግዚአብሔር ስጡ" (፪ዜና ፴፥፰)

Click here to read in PDF
ከሰንበት //መምሪያ ድረ ገጽ የተገኘ
ከዶ/ አምሳሉ ተፈራ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፊሎሎጂ ዲፓርትመንት
ረዳት ፕሮፊሰር
ለሁሉ ፈጣሪ ለእግዚአብሔር ራስን መቀደስና ከኃጢአት መለየት ለሰው ሁሉ የቀረበ ጥሪ ነው። ይህን ዘንግተው የነበሩ ሕዝበ እስራኤል ወደ አምላካቸው እንዲመለሱና ሁለንተናቸውን ለእርሱ እንዲሰጡ የተላከላቸው መልእክት ነው ርእሳችን እኛንም ይመለከታልና እንደሚከተለው በዝርዝር እንየው።
የሚታየውንም የማይታየውንም የፈጠረ፣ በባሕርም በየብስም ያሉትን ያስገኘ፣ ሰውን ለክብሩ ወራሽነትና ለስሙ ቀዳሽነት የወሰነ፣ ዓለምን ሲፈጥር አማካሪ ያልፈለገ፣ ፍጡሩን በመመገብና በመውደድ ወደር የሌለው፣ ለሰው ልጆች ራሱን አሳልፎ የሰጠ ነው ቸሩ አምላካችን እግዚአብሔር። ይህን ጌታ በምንም ልንለውጠውና ልንተካው አንችልም። አምላክ ነውና ተወዳዳሪ የለውም (ኢሳ. ፵፣ ፲፪ - ፲፬)
የርእሳችን መነሻ የሆነው «እጃችሁን ለእግዚአብሔር ስጡ» የሚለው ትምህርት የተሰጠው፣ ሃያ ዘጠኝ ዓመታት በእስራኤል ላይ በነገሠው ንጉሥ ሕዝቅያስ ነው። ምክንያቱ ደግሞ የእግዚአብሔርን ፋሲካ ለማድረግ የሚደረግ ቅድመ ዝግጅትን ይመለከታል። እግዚአብሔር ንጹሐ ባሕርይ ስለሆነ፤ ወደ እርሱ መቅረብና ማገልገል የሚቻለው በንጽሕና ሆኖ ነው፤ አገልግሎትንም የሚቀበለው ያለቸልታ በትጋት ሲሆን ነው። «ልጆቼ ሆይ በፊቱ ትቆሙና ታገለግሉት ዘንድ፥ ታጥኑለትም ዘንድ እግዚአብሔር መርጦአችኋልና ቸል አትበሉ፤ ብሎ ያዘዘን ለዚህ ነው (፪ዜና. ፳፱፣፲፩)
«
ንጉሡ ሕዝቅያስ ለእግዚአብሔር ፋሲካ እንዲደረግ ወደ እስራኤልና ወደ ይሁዳ ለዐሥራ ሁለቱም ነገደ እስራኤል መልእክት ላከ። ነገር ግን ካህናቱ ገና በሚገባ ስላልተቀደሱ፣ ሕዝቡም በኢየሩሳሌም ተጠቃለው ስላልተሰበሰቡ፤ ፋሲካው በደንብ ሲዘጋጁ በቀጣዩ ወር እንዲከበር ተወሰነ። ለቀጣዩ ወር ግን ሁሉም ከያለበት ከዳን እስከ ቤርሳቤህ ድረስ እንዲሰባሰብ እንዲህ የሚል ዐዋጅ ተነገረ፣ «የእስራኤል ልጆች ሆይ ... እግዚአብሔርን እንደ በደሉ እንደ አባቶቻችሁና እንደ ወንድሞቻችሁ አትሁኑ። አባቶቻችሁም እንደ ነበሩ አንገተ ደንዳና አትሁኑ፤ እጃችሁንም ለእግዚአብሔር ስጡ፤ ለዘላለም ወደ ተቀደሰው ወደ መቅደሱም ግቡ፤ ጽኑ ቁጣው ከእናንተ እንዲመለስ አምላካችሁን እግዚአብሔርን አምልኩ። (፪ዜና ፴፣፯-)