(http://awdemihreet.blogspot.com/)ባለሁለት ሚስቱ እና ፈቱ ዳንኤል
ክብረት ያፈረሰ ሰው የሚገባውን ማርገጃ አድማቂነት እምቢኝ ብሎ ባልተማረው ትምህርትና በማይመልሰው ተሰጥኦ “ዲያቆን” ተብሎ ለእርሱ
ብጤ ጨዋ ማኅበርተኞቹ “ሊቅ” ሆኖ እና “ሊቅ” ተሰኝቶ ከእውነተኛ የቤተክርስቲያን ሊቃውንትና አባቶች ሸሽቶ እንደ እርሱ በሁለት
ሀሳብ በገንዘብ እና በዝሙት ከሚያነክሱ አባ አብርሃም እና አባ ኤዎስጣጢዎስን ከመሰሉ ግለሰቦች ተጠግቶ በአድርባይ ብዕሩ እነዚህን
የጉድ ሙዳዮች እየሸላለመ የነበረበት ሁኔታ አልበቃ ብሎት አሁን ደግሞ የአውስትራሊያ አህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ለመሆን ደፋ
ቀና እያለ ነው፡፡
ማህበርዋን በዋና ጸሐፊነት በመራባቸው
ረጅም አመታት ከየዋኃን አባላት ከሚሰበሰበው ገንዘብ እና ከቤተክርስቲያን የድርሻውን ወስዶ በሲኤምሲ ሁለት ቤቶችን የሰራው እና
እና ከጊፍት ሪል እስቴት አንድ ቤት በመግዛት የሦስት ቤቶች ባለቤት የሆነው ዳንኤል ክብረት አሁን ደግሞ ሌላ ሦስት ቤት የሚሰራበትን
ገንዘብ ከቤተክርስቲያን ለመዝረፍ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ ይህንን ለማሳካት በሲአይኤ ወኪልነት በሚታወቀው እና እንደ እባብ ልስልስ
ገላውን እያሳየ የተንኮል ድሩን በሚያደራው እና በቅርቡ የማኅበሩን አንጃ በሀሳብ የተቀላቀለው በአቶ ባያብል አማላጅነት ጉዳዩ
መስመር የያዘለት የመሰለው ዳንኤል ለቅርብ ወዳጆቹ የአውስትራሊያ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ የመሆኑ ጉዳይ ያለቀለት መሆኑን ሲናገር
ተሰምቷል፡፡ በዚህም ተቋርጦ የነበረው የዳንኤል እና የባያብል ፍቅር የታደሰ መስሏል፡፡