Thursday, May 31, 2012

የጠላት ከፍታ


Click here to read in PDF            ከቤተ ጳውሎስ ብሎግ የተወሰደ
ጴጥሮስና ዮሐንስ በተሰጣቸው ጸጋ በተአምራት ወደ ላይ ሲወጡ ያየው ሲሞን መሠርይ እኔም እንደ እነርሱ ማድረግ እችላለሁ ብሎ በምትሐት ወደ ላይ ከፍ ሲል ጴጥሮስና ዮሐንስ ከታች ወደ ላይ ሲመጣ አዩት፡፡ ጴጥሮስም ችኩል ነውና እናማትብበት አለ፡፡ ዮሐንስ ግን “ከፍ ከፍ ይበል ለአወዳደቁ እንዲመች” አለው በማለት አንድ መምህር በልጅነቴ አጣፍጠው የነገሩኝን አልረሳውም፡፡

ሙሴ የሠራውን ተአምራት የሚመስል የፈርዖን ጠንቋዮች ሠርተዋል /ዘጸ. 7፡8-13/፡፡ የሙሴ ተአምራት ግን አሸንፏል፡፡ ምክንያቱም በእግዚአብሔር ሥራ ፊት የሰይጣን ሥራ ስለማይቆም ነው፡፡ የበኣል ነቢያት በኣል ሆይ ስማን እያሉ ሲጣሩ ውለዋል፡፡ ለወትሮ የሚሰማቸው መንፈስ ዛሬ ግን ቀርቦ ምንም ሊያደርግ ያልቻለው የእግዚአብሔር ሰው ኤልያስ በዚያ ስለነበረ ነው /1ነገሥ. 18፡25-29/፡፡ መንፈሳዊውን ዓለም እየታከከ የሚኖር ጥገኛ መንፈስ አለ፡፡ ሰይጣን ራሱን ችሎ መቆም አይችልም፡፡ ስለዚህ በእግዚአብሔር ተግባር ትይዩ አስመሳይ ተአምራቶች በማድረግ አምልኮን መጋራት ይፈልጋል፡፡ ሰይጣን ካዱ ከሚል የነገሥታት አዋጅ ይልቅ እምነት በሚመስል ምዋርት ብዙ ውጤት እንደሚያገኝ ያውቀዋል፡፡

ብዙ ጊዜ የተቃዋሚዎቻችን ከፍታ ይረብሸናል፡፡ የጠላት ከፍታ ለመውደቅ መሆኑን ግን የሚያውቁ በመንፈስ ቅዱስ የሚመሩ ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡ በሥራችን ስኬታማ ካለመሆናችን ይልቅ የሚረብሸን የጠላቶቻችን ጊዜያዊ ድል ነው፡፡ ውጤታማ ነን ብለን የምንለካው በራእያችን መሳካት አይደለም፡፡ የጠላትን ሬሣ ካላየን ውጤታማ ነኝ ለማለት አንደፍርም፡፡ ጌታ እንደ በጎች በተኩላዎች መካከል ልኮናል እንጂ በተኩላዎች ሬሣ መካከል አልላከንም /ማቴ.10፡16/። ጠላትም አለ እኛም እንኖራለን። እግዚአብሔር ለእባቡ አሳብ እንጂ እግር አልሰጠውም። ጴጥሮስ የሆነው ማንነታችን ግን ቶሎ እርምጃ ለመውሰድ ይፈልጋል፡፡ በራሳቸው ሊጠፉ የነበሩ የጠላት ሰፈሮች በመነካካታቸው እንደገና ተቆስቁሰው እናያለን፡፡ ያለጊዜው የሆነ እርምጃ ለጠላት ህልውናን የሚጨምር ነው፡፡ ዮሐንስ የሆነው ማንነት ግን በትዕግሥት ሆኖ ከፍታው ለውድቀት መመቻቸት መሆኑን ያውቀዋል፡፡ ምክንያቱም ያለ እግዚአብሔር ከፍ ያሉ ይዋረዳሉና። ቃሉ፡- “ከእግዚአብሔር ጋር የሚጣሉ ይደቅቃሉ፤ … ለንጉሡም ኃይል ይሰጣል፤ የመሲሑንም ቀንድ ከፍ ከፍ ያደርጋል” ይላል (1ሳሙ. 2÷10)፡፡

Wednesday, May 30, 2012

የማኅበረ ቅዱሳን ጉዞና የዋልድባ ሰልፍ ግጥምጥሞሽ

Click here to read in PDF
ማኅበረ ቅዱሳን የሚባል ሰሙ መንፈሳዊነት ወርቁ ደግሞ ፓለቲካ የሆነ ድርጅት ፖለቲካዊ ትርፍ ያስገኝልኛል ብሎ የሚያምናቸውን መንፈሳዊ መሰል ጉዳዮችን እንዴት አድርጎ እንደሚጠቀምባቸው ሴራ ሲሸርብ ውሎ እንደሚያድር ይታወቃል። መንግስት የጀመረውን የዋልድባ አካባቢ የስኳር ፕሮጀክትን እንደ ጥሩ ፖለቲካዊ ትርፍ ማግኛ ለመጠቀም በትጋት እየጣረ ያለው ድርጅት በተለያየ ብሎጎቹ ላለፉት አራት ወራት ሳይታክት ከፍተኛ የሆነ ቅስቀሳ አደርጓል። በዚህም በተለይም ሁሌ ቀድሞ የጮኸን እውነተኛ ብሎ የሚያምነውን የሕብረተሰብ ክፍል ልብና ቀልብ ለመግዛት ችሏል። የዋልድባ አካባቢ የስኳር ድርጅት ከገዳሙ ክልል የራቀ እና ገዳሙን በቀጥታ የጎዳበት ምንም አይነት ጉዳት የለም ብሎ ያረጋገጠውን የኅብረተሰብ ክፍል በአዲሱ የዜና ማሰራጫዋ ኢሳትና በብሎጎችዋ ማኅበርዋ አጥብቃ እየተቃወመች ነው ያለችው።
በተለይም ከመሰላቸው የሁለት ሰዎችን ቆሞ ማውራት እንኳ ተአምር ለማለት የማይመለሱት የአንድአድርገን ብሎግ አዘጋጆች ጉድ ጉድ እያሉ ተአምር ተአምር አረ ስሙ ተአምር በማለት የህብረተሰቡን ልብ ለማሸፈት ሮጠዋል። ነገሩ የፈለጉትን ያህል አልደምቅ ሲል ደግሞ ህዝብ ወደ ዋልድባ እየተመመ ነው የሚል ቅስቀሳ ወደ ዋልድባ እንደ ሁልጊዜው ለንግስ የሚሄደውን የኅብረተሰብ ክፍል ለሌላ አላማ የሄደ በማስመሰል ሌላው የኅብረተሰብ ክፍል እኔስ ለምን ይቅርብኝ ብሎ ለመስዋዕትነት እንዲወጣና ደም መፋሰስ እንዲከሰት ከፍተኛ ቅስቀሳ አድርጎ የነበረ መሆኑ አይዘነጋም። ወዲያውም ክተት ወደ ዋልድባ የሚል ፖስተር አዘጋጅቶ በማኅበሩ አመራሮችና አባለት ማለትም ብርሃን አድማሴ ህብረት የሺጥላ እና ሌሎችም ፌስ ቡክ ገጽ ላይ በመለጠፍ ግልጽ የሆነ የጦርነት አዋጅ አውጇል።

Tuesday, May 29, 2012

ኢካቦድ: ከመሰደድ ይልቅ ማሳደድን ለመረጠ ሲኖዶስ!!

   Click here to read in PDF                                                     በዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል

በዚህ ርዕስ ውድቀትን የሚያበሰር፣ ሰላምንና መረጋጋትን እንደ ሰማይ ከዋክብት የሚያርቅ በፈንታው ሁከትንና የሽብር ድርጊት የሚያሰፈን፣ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን ውድቀት በሚጠባበቁ ልሂቃን ከብዙ ዓመታት በፊት የታቀደውን ዕቅድ ተግባራዊነት የሚያረጋግጥ፣ ወንጌላውያንም በማሳደድ ወንጀለኞች ለመሾም የተላለፈውን ውሳኔና የሚያስከትለውን ውድቀትና ድቀት አንስተን በጥልቀት እንዳስሳለን። መንሸራሸሪያ ሀሳባችንም በወርሐ ግንቦት 15/2004 የተጠናቀቀውን የሲኖዶስ ስብሰባ በተላለፈው ባለ አስር ነጥብ የአቋም መግለጫ በተለይ በተራ ቁጥር ስድስት ላይ  የሰፈረው ይኸውም ራሱን “ማህበረ ቅዱሳን” በማለት ስለሚጠራ አጽራረ ቤ/ያን በተመለከተ የተላለፈውን ጊዜያዊ ውሳኔ ይሆናል።
“የዔሊም ልጆች ምናምንቴዎች ነበሩ፤ እግዚአብሔርንም አያውቁም ነበር፤ የካህናትም ልማድ በሕዝቡ ዘንድ እንዲህ ነበረ፤ ሰው ሁሉ መሥዋዕት ሲያቀርብ ሥጋው በተቀቀለ ጊዜ የካህኑ ሎሌ ይመጣ ነበር፥ በእጁም ሦስት ጣት ያለው ሜንጦ ነበረ፤ ወደ ድስቱም ወይም ወደ ምንቸቱ ወይም ወደ አፍላሉ ወይም ወደ ቶፋው ይሰድድው ነበር፤ ሜንጦውም ያወጣውን ሁሉ ካህኑ ለእርሱ ይወስደው ነበር። ወደዚያም በመጡት በእስራኤላውያን ላይ በሴሎ እንዲህ ያደርጉ ነበር፤ ደግሞም ስቡን ሳያቃጥሉ የካህኑ ሎሌ መጥቶ የሚሠዋውን ሰው። ጥሬውን እንጂ የተቀቀለውን ሥጋ ከአንተ አይወስድምና እጠብስለት ዘንድ ለካህኑ ሥጋ ስጠኝ ይለው ነበር፤ ሰውዮውም አስቀድሞ ስቡን ያቃጥሉት ኋላም ሰውነትህ ደስ የሚያሰኛትን ትወስዳለህ ቢለው፥ እርሱ አይሆንም፥ ነገር ግን አሁን ስጠኝ፤ እንቢም ብትል በግድ እወስደዋለሁ ይለው ነበር ሰዎቹም የእግዚአብሔርን ቍርባን ይንቁ ነበርና የጎበዛዝቱ ኃጢአት በእግዚአብሔር ፊት እጅግ ታላቅ ነበረች። መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 2: 12

አፍኒን እና ፊንሐስ (“ማህበረ ቅዱሳን”):
v የእግዚአብሔርን ህግ በመናቅ ቅድሚያ መሰጠትና መቅረብ የሚገባውን የእግዚአብሔር መስዋዕት ትተው ቅድሚያውን ለራሳቸው ይሰጡ እንደ ነበር፣ 1ኛ ሳሙ. 2: 16-17
v የመስዋአቱን ስርኣት ያስተጔጉሉ እንደ ነበር፡
v በመገናኛው ድንኳን ከሚያገለግሉ ሴቶች ጋር የክብሩ ዙፋን ባለበት በእግዚአብሔር ማደሪያ ውስጥ ያመነዝሩ እንደ ነበር፡
v አስፀያፊ የከነዓናውያን የቤተ ጣዖት ዓይነት አምልኮ ይፈጽሙ እንደነበር:
v እንዲሁም የዔሊ ልጆች ምግባረ ብልሹዎች ከመሆናቸው በተጨማሪም ሌቦች እንደነበሩ ነው። (ቁ. 17)

Monday, May 28, 2012

እውን “ማኅበረ ቅዱሳን” (ሰለፊያ) እየተዘጋ አይደለምን???

Click here to read in PDF
አንዳንድ የዚህ ክፉ ነብሰ በላ የሆነ ድርጅት አመራሮችና አባለት “አባሠረቀንና አቡነ ጳውሎስን ብንገድል መንግስተ ሰማያት መግባታችን አይቀርም እንጸድቃለንም። በዚህ አንጠየቅም” እያሉ ሲያወሩ ስንሰማ ግራ እየገባን ይህ ከምን የመጣ አመለካከት ነው? መጽሐፍ ቅዱስ የማይደግፈውን አስተሳሰብ እንዲህ በድፍረት የሚናገሩት ለምንድን ነው እያልን ለአመታት የቆየን ቢሆንም በስተመጨረሻ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲህ የሚሉት ለምን እንደሆነ በግልጽ ነግረውናል። እኛም ነገሩ ገብቶን ሰው በመግደል ገነት እንደሚወርሱ የሚያምኑ ሰለፊዎች መሆናቸውን አረጋግጠን ከየትኛው መጽሐፍ ይህን ትምህርት እንዳገኙት አውቀናል። ከማቅ ሰዎች ጋር በሀሳብና በአመለካከት ብቻ የተለያየን መሰሎን የነበረ ቢሆንም በምንመራበት መጽሐፍም ቢሆን ልዩነት እንዳለን አውቀናል።
ከዚህ እውነት በመነሳት “ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር” እንዲሉ በግንቦት ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ የታዩ ክስተቶችን የተመለከተ ትንታኔ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቶአል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እራሱን በቅዱሳን ስም “ማኅበረ ቅዱሳን” በሚል የሰየመው የፖለቲካ ድርጅት ለአለፉት ሁለት አሥርት አመታት በቅድስት ቤተክርስቲያናችንም ሆነ በሀገራችን ኢትዮጵያ ላይ እያደረሰው ያለውን አሉታዊ ተጽእኖ ሁሉም የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የሚያውቁት ሐቅ ነው፡፡

Sunday, May 27, 2012

አባ ሳሙኤልና ሚጡ


መቼም በዚህ ወር ቤተክርስቲያናችን ያላስተናገደቸው ጉድ የለም። አባቶቻችን በቁም ነገር ያሳልፉታል ብለን የገመትነው ስብሰባ ገና ከመነሻው በጋዜጣ መንፈሳዊ ሰዎች ነን እያላችሁ ለሁሉ ሞተናል በሚል ሥርዓት ውስጥ አልፋችሁ ስታበቁ ለምን ሀብት ታከማቻላችሁ? ለምን አትከባበሩም እንደ መንፈሳዊ ሰው አንዱ አንዱን መሸከም ለምን ይከብደዋል? በአባቶቻችን ዘንድ ያልነበረ በእናንተ እንዴት ተከሰተ? ደሞ መጽሐፍ አገራችሁ በሰማይ ነው ሲል እናንተ አረ የለም በአሜሪካ ነው እያላችሁ ዜግነትን ታከማቻላችሁ ተው እንዲህ ያለውን ነገር!! ሥርዓት አፍርሳችሁ ሀብት ታከማቻላችሁ ሀብት ለቤተክርስቲያን ማውረስ ሲገባችሁ ለሥጋ ዘመድ ታወርሳላች!! ግድ የለም አባቶቼ ንስሐ ግቡ የሚያዋጣው እሱ ነው ተባልን ብለው ጣራ እየቧጠጡ ንዴት አስክሯቸው በማኅበርዋ አጋፋሪነት የጋዜጣው አዘጋጆች ካልተወገዙ እያሉ አራት ቀን ሙሉ ስለጋዜጣ ያወሩባት ተዓምረኛ ወር ነች።
ደግሞም እንዲሁ  በዚህ ወር ማኅበሯ ራስዋን ከፍ ከፍ አድርጋ እንደ ሳጥናኤል ወደ ላይ ቀና ብላ እያየች ከኔ በላይ ሌላ አለ እንዴ? እያለች መጠየቅ ጀመረች ወር ናት። ይኸው በቤተክርስቲያኒቱን ነገስኩባት እኮ መሻቴ ተፈጸመ እንግዲህ ራስ ሆንኩዋት እያለች በውስኪ ጠርሙስ በኩል ራስዋን ማየት የጀመረችበት ወርም ነው። እንደሚታወቀው በውስኪ ጠርሙስ በኩል የሚታይ ነገር አቅልን አሳጥቶ ራስን አስቶ ከመስመር የማስወጣት አባዜ እንዳለሁ በልምምድም በተሞክሮም የሚበልጡን የማኅበሯ ሰዎች አይስቱትም። እኛማ እንዲህ ያለው ነገር የማይነካካን የእኛም ሆነ የቤተክርስቲያን ራስ ማን እንደሆነ አሳምረን የምናውቅ እና እሱን የምናከብር ነን። ጌታ በክብሩ ሲመጡበት ምን እንደሚያደርግ በቅርቡ ያሳየናል።

Saturday, May 26, 2012

«ወሶበሂ ይነብብ ሐሰተ እምዚአሁ ይነብብ….ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል»

                                       በመምህር ፈንታ/ fennate@gmail.com/
የማኅበረ ቅዱሳን አፈቀላጤ የሆነው ደጀ ሰላም በወርሃ መጋቢት መጨረሻ ላይ የሚከበረውን የመድኃኔዓለም ዓመታዊ በዓል አስታኰ በዛሬማ ወንዝ ላይ እየተገነባ ያለውን የመንግሥት የስኳር ልማት ለማጥናት ሳይሆን ለሽብር ፍጆታ የሚሆን መረጃ ለመሰብሰብ የማኅበሩን አባላት በተሳላሚ ሽፋን ወደ ገዳሙ ከላካቸው አባላቶቹ የተገኘውን ዘገባ ደጀ ሰላም በገጹ አውጥቶ ነበር።
የስኳር ልማቱን ለማስቆም ሕዝቡ ለጦርነት ተመመ፤ መንግሥት አካባቢውን ለቆ ወጣ፤ ፖሊሶች አለቁ፤ ሬሳ ቆጠራው ቀጥሏል …..ወዘተ የብስጭት ማስተንፈሻ ስሜቶቻቸውን ከልካይ በሌለበት ድረ ገጽ ውሸቱን በቆርጦ ቀጥል ጥበባቸው  እንቶ ፈንቶአቸውን አስነብበውናል።
አሁን ደግሞ ጉዳዩ በወሬ የማይቆም መሆኑን ሲያረጋግጡ ለጫወታ ወግ ፍለጋ ጥቂት ጊዜ እረፍት የወሰዱ መስለዋል። አንድ ነገር ፈጥረው የሽብር ዜና እስኪያሰሙን ድረስ የሚያስተምሩት የወንጌል ቃል ስለሌላቸው ጥሩ የእረፍት ጊዜ ይሁንላችሁ ብለናቸዋል።
ይህንን ያህል ለመግቢያ ካልን የጽሁፋችን ርእስ ወደ ሆነው ጉዳይ እናምራ። ከሁከት ውጪ ነገረ መለኰትን የማያውቁ ሽፍቶች» በሚለው ጉዳይ ተንተርሰን ወደ ርእሳችን ስንገባ ደጀ ሰላም በተሳላሚ ሽፋን በማቅ አባላቶቿ ያስጠናችው  የጥናት አንዱ ክፍል በዋልድባ ገዳም «የዘጠኝ መለኰት አማኞች» መኖራቸው መዘገብ ነበር።   ስለዋልድባ መነኰሳት መናፍቅነትና ክሃዲነት ያገኘሁት ውጤት ነው በማለት  በስኳር ጥናቱ ለውሶና ስኳር አድርጎ በማቅረብ ስለዘጠኝ መለኮት አማኞች ሊያስነብበን ፈልጎ ይህንኑ በኢንተርኔት ላይ ሰቅሎት አግኝተናል።
ከጽሁፏ የተወሰደው  ዘገባዋ ይህንን ይመስላል

ይሁን እንጂ እነ በጋሻውን፤ እነ አባ ሠረቀ ብርሃንንና ሌሎችንም ሁሉ በአንድ ሙቀጫ አስገብታ በተሐድሶ ስም የምትወቅጠው ይህች ብሎግና ማኅበር ድሮውን በፈጠራና ስም በማጥፋት ላይ ተመስርታ እንጂ የሃይማኖት እውቀት ስላላት በዚያ ላይ ተመስርታ ወይም የመናፍቃን ጉዳይ የሚያሳስባት ሆኖ አይደለም።

Friday, May 25, 2012

ማን ይሆን እውነተኛ? “ለማህበረ ቅዱሳን” የተሰጠ ምላሽ:

Click here to read in PDF
(ውንድማችን ዲ/ን ሙሉጌታ ደጀ ሰላም የማኅበረ ቅዱሳን ለመሆንዋ “ልሳነ ሌዋታን “ደጀ ሰላም” የማን ናት?” በሚል ርዕስ በበቂ ማስረጃ የተደገፈ ጽሁፍ በዚህ ድረ ገጽ ማውጣቱ ይታወቃል። ይህን ተከትሎ የማቅ ሰዎች ስንሸፍነው የነበረው እውነት ተገለጸ በማለት ድንጋጤና ፍርሀት በተቀላቀለበት መልኩ የእኛ አይደለም በማለት እየተሯሯጡ ይገኛሉ። ማኅበርዋ አርቃ ሳትመትር በብሎጉ ላይ ያወጣችው ጽሁፍ የሚያስከትልባትን ችግር ውላ አድራ መገንዘብ በመቻሏ ጽሁፉን ለመሰረዝ ብትሞክርም ጎግል ግን እውነትን መግለጽ ስለማይቸግረውና አንዴ ተጭኖ የነበረ ነገር ሲወጣ/ሲሰረዝ ምን እንደ ተደረገ የሚገልጽበት መንገድ ስላለው የማኅበረ ቅዱሳንን የእኛ አይደለም ጫጫታ ሊያግዝ አልቻለም። የማቅ ሰዎችም ዋናውን ማረጋገጫ ትተው በተጨማሪ ማስረጃነት የቀረቡ ጹሁፎችን ለመቃወም ሞክረዋል። ቀድሞ ሲጠየቅ ይኸው ብሎ ከተፍ ያደርገው የነበረውን     ጽሁፍ ሲሰረዝ ደግሞ ተሰረዘ ማለቱ አናዷችሁ ጎግልን በተሀድሶነት ሳትጠረጥሩትም አልቀራችሁ? ሲል የሚጠይቀው ዲ/ን ሙሉጌታም የእኛ አይደለም የሚል የካፈርኩ አይመልሰኝ ጫጫታችሁን ከቀጠላችሁ የእናንተ እንደሆነ አብራርቼ ልግለጽላችሁ ብሎ ይሄን ድንቅ ጽሁፍ ጽፏል።)
የሀገሬ ሰው ቅጥፈት የለመደች እጅ ከንስሃ ይልቅ ለዓመጽ ቅርብ ነች። እንዲል ይህ ነፍሰ ገዳይ ሳለ ራሱን “ማህበረ ቅዱሳን” በማለት የሚጠራ ድርጅት ስሙ የማይጠራ አጋንንት የነገሰበት “የጎበዝ” ስብስብ በስህተት ላይ ስህተት፣ በውሸት ላይ ውሸት፣ በአመጽ ላይ አመጽ መስራትና መደጋገም ሁነኛ መታወቂያው ለመሆኑ ማናችንም አንስተውም። ይህን መሰሉ የማህበሩ (“የማህበረ ቅዱሳን”) መሰሪ ድርጊት በማጋለጥ ረገድም ጸሐፊው “ደጀ ሰላም” በመባል የሚታወቀው የሽብርና የሁከት ማእከል መካነ ድር “የማህበረ ቅዱሳን” ለመሆኑና ማህበሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያንና አገልጋዮችን በተቀናጀ መልኩ ማተረማመስ እንዲሁም ማሳደድ  እየተያያዘው ሲመጣ የቀድሞ ስራዎቹ(ባለቤትነቱን የሚመሰክሩና የሚያረጋግጡ) ከስፍራው በመንቀል የእኔ አይደለም በማለት እስከ መካድ ደርሷል። በዚህም ሳይመለስ የሚያቀኝ የለም በሚል የሞኝ ፈሊጥም እስከ ዛሬው ዕለት ድረስ ያለውንና የሌለውን አቅም በመጠቀም ከወትሮ በበለጠ ሁኔታ ሰማያዊትና ቅድስት በሆነችው ቤ/ያን ላይ ሽብርንና ሁከትን በመዝራት ረገድ እየገፋበት እንደሚገኝ በመግለጽ ከጥቂት ቀናት በፊት የሚከተለው ጽሁፍ ለንባብ መብቃቱ ይታወሳል።

“ይህ የሚመለከቱት መረጃ “ደጀ ሰላም” በመባል የሚታወቀውን ድረ-ገጽ/ብሎግ ሲጀመር ማኅበሩ የራሱ እንደሆነ በይፋ በድህረ ገጹ የገለጸበት/ያስተዋወቀበት በእንግሊዝኛ የድረ-ገጹ የመጀመሪያ የጽሑፉ “ሊንክ” ነበር። በተለይ deje-selam.blogspot.com/…/Ethiopia-mahberekidusan-eotc-past.html- የሚለውን ጽፈው ለመጎልጎል የሞከሩ እንደሆነ “ጭራሽ ከስፍራው ተነቅለዋል” የሚል መልስ ነው የሚያገኙ ለምን? ማኅበሩ ስራዬ ብሎ ቅድስት ቤተ-ክርስቲያንን መዋጋትና ማፍረስ ብሎም ቅድስት ቤተ-ክርስቲያንና የአባቶችን ክብር በሚነካ መልኩ ከአንድ በኢትዮጵያዊ ባህልና ወግ ያደገ ፍጡር በማይጠበቅ ልቅነትና ዋልጌነትን በእጅጉ አይለው በሚታዩበት ሁኔታ ማዋረድና ማንቋሸሽ እየተያያዛው ሲመጣ ጽሑፉን ከስፍራው በመንቀል የእኔ አይደለም እስከ ማለት ደርሷል።ድያ  ይህን ቁልጭ ያለውን በማያሻማ አገላለጽና በግልጽ መረጃ/ሰነድ የተደገፈውን ሐቅ ሽምጥጥ አድርጎ ለመካድ የማቅ ሰዎች የሆነውና ያልሆነውን ያልተባለና ያልተጠየቁትም ለመቀባጠር እንቅልፍ አጥተው ሰንብተዋል። በዚህ አጋጣሚ“… ምላሽ” በማለት የቀረበውን የቅጥፈት ስራ ሳይውል ሳያድር በኢ-ሜይል አድራሻዬን የላክህልኝ ወዳጄ መ/ም ደመላው እጅግ አድርጌ ላመሰግንህ እወዳለሁ።

በፍርድ ፈንታ ደም ማፍሰስ በጽድቅ ፈንታ ጩኸት(ኢሳ. 5÷7)፡፡

አንዲት ሕጻን ልጅ ሞታ የጎጃሟ አልቃሽ፡-
                         “ምን ዓይነት ቄስ ናቸው የማይጠብቁ ዕቃ
                         እበተስኪያን ጓሮ እጣኒቱ ወድቃ”
በማለት የሀዘን ቅኔ (ሙሾ) አሰምታለች፡፡ የቄሱ አንዱ ሥራ ዕጣን መጠበቅ ሲሆን ዋነኛው ሥራቸው ግን ሕጻናትን መጠበቅ ወይም ማሳደግ ነው፡፡ ሕፃናት ከቤተ ክርስቲያን አደባባይ ሊቀመጡ አባቶቻቸውን እያዩ ሊማሩ ሲገባ ከቤተ ክርስቲያን ጓሮ ከመቃብር ውስጥ ሲወድቁ ማየት አሳዛኝ ነው፡፡ አልቃሿ በሕፃናት ማለቅ ቀሳውስቱ ለምን አይጸልዩም ማለቷ ሲሆን ከዚያ ባሻገር ግን ትውልድን ለምን ይቀጫሉ? ማለቷ ነው፡፡ አባቶች አደራቸውን ባለመወጣታቸው ትውልዳችን የሞት ልጅ ሆኗል፡፡ ራሱን በራሱ እየመራ የዘመን ምርኮኛ፣ የኃጢአት ግዞተኛ ሆኗል፡፡ ይልቁንም በአባቶች ፈንታ እንዲተኩ ከዐውደ ምሕረቱ ሊቀርቡ የሚገባቸው ወጣቶች እየተገፉ ወደ መቃብር ስፍራ መውረዳቸው ዛሬም ልብ ያለውን የሚያስለቅስ ነው፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስም፡- “አሁን ስለ ወዳጄና ስለ ወይን ቦታው ለወዳጄ ቅኔ እቀኛለሁ” ብሏል (ኢሳ. 5÷1)፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ ለእግዚአብሔር አዝኖ ወዳጅነቱን ለመግለጥ የሀዘን ሙሾ አሰምቷል፡፡ ስለ ወዳጅ ይለቀሳል፡፡ ወዳጅ በሞት ስለተለየ ብቻ ሳይሆን የጠበቀው እንዳልጠበቀው ሲሆንበት ይልቁንም ልጁን በሞት ሲያጣ ለወዳጅ ይለቀሳል፡፡ እግዚአብሔር ሕያው ወዳጅ ነው፤ ነቢዩ ኢሳይያስ ግን ያለቀሰው ሞትን ስለመረጡት ትውልዶች ነው፡፡ እግዚአብሔር መንግሥቱ የማይነካ ነው፤ ነቢዩ ኢሳይያስ ግን ያለቀሰው ከእግዚአብሔር ፍቅር ለተፈናቀሉት ነው፡፡ እግዚአብሔር የማይጎድልበት ነው፤ ነቢዩ ኢሳይያስ ግን ያለቀሰው ሰላማቸውን ስላላወቁ ሕዝቦች ነው፡፡ በእውነት ካጣ ሰው ይልቅ አግኝቶ ያላወቀበት እጅግ ሊለቀስለት ይገባል፡፡ እግዚአብሔርን ያህል ጌታ ለገፉ፣ ገነትን ታህል ቦታ ችላ ላሉ ልቅሶ ይገባል፡፡ ኢሳይያስ ግን ያለቀሰው ለሟቾቹ ሳይሆን ለወዳጁ ለእግዚአብሔር ነው፡፡ የሰው ልጆች እንዳፈቀራቸው አለመገኘታቸው፣ እንዳደረገላቸው አለማመስገናቸውን ባሰበ ጊዜ ለወዳጁ አለቀሰ፡፡
እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያደረገው እንክብካቤ ሊገለጥ የማይችል ነው፡፡ ኢሳይያስ ይህን ሲገልጥ፡- “ለወዳጄ በፍሬያማው ኮረብታ ላይ የወይን ቦታ ነበረው፡፡ በዙሪያው ቈፈረ÷ ድንጋዮችንም ለቅሞ አወጣ÷ ምርጥ የሆነውንም አረግ ተከለበት በመካከሉም ግንብ ሠራ፡፡ ደግሞም የመጥመቂያ ጒድጓድ ማሰበት፤ ወይንንም ያፈራ ዘንድ ተማመነ÷ ዳሩ ግን ሆምጣጣ ፍሬ አፈራ” ይላል (ኢሳ. 5÷1-2)፡፡

Thursday, May 24, 2012

የሲኖዶሱ ስብሰባ ተጠናቀቀ

Click here to read in PDF
በልዩ ልዩ ድራማዎች የታጀበውና በስድብና በከፍተኛ የጥላቻ ስሜት የታጀበው የሲኖዶሱ ስብሰባ በትናንትናው ዕለት ተጠናቀቀ። የመዝጊያው ንግግር ራሱ ራሱን የቻለ ድራማ ተስተናግዶበታል።

በትናንትናው ጠዋት ውሎ የማኅበረ ቅዱሳን ጉዳይ እንደገና ያነጋገረ ሲሆን መተዳደሪያ ደንቡ እስኪሻሻል እስከ ጥቅምት ሲኖዶስ ስብሰባ ብቻ ከሰንበት ማደራጃው ተለይቶ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ ሥር ሆኖ እንዲቀጥል ተወስኗል። አዳዲስ ጳጳሳት እስኪሾሙ ድረስም አቡነ ገብርኤል ቦረናን አቡነ ዮሴፍ ጅጅጋን ደርበው እንዲሰሩ ተወስኗል። አቡነ ሳሙኤል ከልማትና ክርስቲናዊ ኮሚሽን በተጨማሪ ትንሳኤ ዘጉባኤንና የቤተክህነት ቤቶችን ያስተዳድሩ የሚል ሀሳብ ቢቀርብም ገጠሩን እንኳ አይተውት ኣያውቁ ቦረና ቢሄዱ ምናለ? የሚል ሀሳብ በመቅረቡ ሁሉ ቀርቶ በልማትና ክርስቲያናዊ መምሪያ ብቻ እንዲያስተዳድሩ ተወስኗል።
የመዝጊያው ሥነ ሥርዓት አዲስ ድራማ ያስተናገደ ሲሆን ጋዜጠኞች ከተጠሩ በኃላ የሚነበበው ጽሁፍ እኛ ያዘጋጀነው ነው ብለው እነ አባ አብርሃም ከማኅበረ ቅዱሳን ቢሮ አስጽፈው ያመጡት መግለጫ እንዲነበብ በመፈለጋቸው መግለጫው ለሰዓታት ተጓቷል። ተጽፎ  የመጣው መግለጫ የማኅበሯን ጽድቅ የሚዘረዝርና ማኅበርዋ ለሀገርም ለቤተክርስቲያንምም ተቃሚ ስለሆነች ማንም ሊቃወማት አይችልም። የሚል ይዘት ያለው እግረ መንገድም መንግስትን ለመጎንተል ያለመ ነበር። ቅዱስነታቸው ግን በሲኖዶስ ስብሰባ ማጠቃለያ ላይ ስለአጠቃላይ የስብሰባው ሂደት ነው እንጂ ስለ አንድ ማኅበር አልዘግብም በማለታቸው መግለጫው የዘገየ ሲሆን በመጨረሻም መግለጫው ተሻስሎ እርሱን አንብበዋል።

Wednesday, May 23, 2012

ሲኖዶሱ የሚመራው በማን ነው? በፓትርያርኩ ወይስ?


Click here to read in PDF
የሰሞኑ የሲኖዶስ ስብሰባን ሂደት ላየ ሊለው የሚችለው ብዙ ነገር ይኖረዋል። በተለይ በስብሰባ ላይ በተነሳ ሀሳብ ሁሉ ላይ ከውጭ ካለው አየር ምክር የሚሹ አንዳንድ ጳጳሳት አካላቸውን ሲኖዶሱ ላይ አድርገው ልባቸው ማኅበረ ቅዱሳን ቢሮ ውስጥ አስቀምጠው በማቅ ሳንባ ነው የሚተነፍሱት፤ የሚተነፍሱበት አየር ደግሞ በልዩ ሁኔታ ማንያዘዋል በሚል ኬሚስት የተሰራ ነው። ይህ ታዋቂ ኬሚስት የሚቀምመው ነገር የሚባል ኬሚካል ሲሆን በመጀመሪያ የሚሞክረውም አባ ሳሙኤል የሚባሉ ባለመንታ ችግር ጳጳስ ላይ ነው። እሳቸው ላይ በትክክል እንደሰራ ሲያውቅ እሳቸውን አስጨብጦ በእለቱ በየሚተነፍሱት አየር ለሚያጥራቸው ሌሎች ጳጳሳት ይልከዋል።
ከዛማ ገበርዲኑን ለብሶ ቤተ ክህነት ግቢ ላይ መዞር ነው። ከዛ ጋሻ ጃግሬዎቹ ሲከቡት የዛሬ አጀንዳ ይህ ይህ ነው የሚወሰነውም ይሔ ነው እያለ ራሱን በመንፈስ ቅዱስ ቦታ አስቀምጦ ያወራል። ማታ ላይም የኮሌጁ ምሩቃን ቢሮ ላይ መብራት አጥፍቶና መጋረጃ ጋርዶ ሰው የሌለ አስመስሎ ይቀመጣል እንዲህ እንደሚያድርግ የሚያውቁ የኮሌጁ ተማሪዎች ታድያ ማንያዘዋል የሚባል የሌሊት ሰይጣን አለ ብለው “በመፍራት” ወደ ምሩቃኑ ቢሮ አካባቢ አይሄዱም። 

ቅዱስ ሲኖዶስ በታሪክ ፊት ተጠያቂ የሚሆንበትን ስህተት ፈጸመ

Click here to read in PDF
  • ውሳኔው አባ ሰረቀብርሃንና ዲ/ን በጋሻው አይመለከትም
  • ማቅ ከሰንበት ማደራጃ ውጭ ሆኗል
  • የአዳዲስ ጳጳሳት ሹመትንም በሐምሌ ሲሰባሰቡ እንደሚፈጸም ታውቋል፡፡

ማህበሩ በተሀድሶነት የከሰሳቸው ግለሰቦች ጉዳይ በተገቢው መንገድ ተጠንቶ ስላልቀረበና ግለሰቦቹም ተጠርተው ስላልተጠየቁ እንዲሁም ምላሻቸው ስላልተሰማ፣ ጉዳዩ በዚህ የህግ አግባብ ተሰርቶ ወደፊት እንዲታይ የተባለውን፣ አቅላቸውን በሳቱና የሚያደርጉትን በማያውቁ ጳጳሳቱ አማካኝነት ማኅበረ ቅዱሳን  አስገልብጦ ግለሰቦችንና ማኅበራትን የሚመለከተውን ውሳኔ ወሰነ፡፡ በዚህም ሲኖዶሱ በታሪክ የሚጠየቅበትን ታሪካዊ ስህተት ፈጽሟል፡፡
ምንም እንኳ ይወገዙ ከተባሉት ውስጥ ከዚህ ቤተክርስቲያን የተለዩ፣ ኦርቶዶክሳውያን ያልሆኑና እራሳቸውም ኦርቶዶክሳውያን አይደለንም ብለው አፋቸውን ሞልተው የሚናገሩ ማኅበራትና ግለሰቦችንን ቀላቅሎ ያቀረበ መሆኑ የታወቀ ቢሆንም አላማው ያደረገውም በእነርሱ አስታኮ እውነተኞቹን የቤተክርስቲያን ልጆች መምታት እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ቤተክርሰቲያኒቷ መኖርዋን እንኳ የዘነጉ ግለሰቦችና ማኅበራት ተወገዙ አልተወገዙ ምንም አይነት ጥቅም እንደሌለው የሚያውቀው ማቅ እነርሱን አስታኮ አውነተኞቹን የቤተክርስቲያን ልጆች ለማስጠቃት ያደረገው ሙከራ ተሳክቶለታል፡፡
ጉዳያችንን በትክክለኛ መንገድ አልታየልንም፡፡ ተጠርተን እንኳ አልተጠየቅንም፡፡ ክሳችን ምን እንደሆነ እንኳ አናውቅም፡፡ ሲኖዶሱ የሊቃውንት ጉባኤው አካሄድ ፍትሀዊነት የጎደለው መሆኑን አውቆ ነገራችንን በማስተዋል ይይልን፡፡ ያሉ ሰዎችንም ጉዳይ ቸል በማለት የሲኖዶሱ ለእንዲህ ያለ ውሳኔ መፋጠን በታሪክ ፊት የሚኖረውን ተጠያቂነት ያጎላዋል፡፡  ማንም ይሁን ማን ቤተክርስቲያን ሊኖራት የሚገባው ድርሻ የመግፋት የማባረር ሳይሆን የማስተማርና የመምከርና መሆን ነበረበት፡፡ ቤተክርስቲያኒቱ ተናግሮ የሚያሳምን መክሮ የሚመልስ አባት የሌላት መሆኑን መረዳቱም እጅግ አሳዛኝ ነገር ነው፡፡ ሰው አጥፍቶዋል በሚል የሀሰት ምስክር ሳይሆን ማጥፋት አለማጥፋቱን በሚያረጋግጥ እውነተኛ ዳኝነት ጉዳዩ ታይቶ መወሰን ሲገባው እንዲሁ በደመ ነብስ በማቅ አሳሳች ባህሪ ተታለው እነርሱ ያጠኑት ይበቃል በማለት ሲኖዶሱ የማኅበረ ቅዱሳን ጉዳይ አስፈጻሚ ሆኖ መገኘቱ ያስተዛዝባል፡፡ 

Tuesday, May 22, 2012

ቅዱስ ሲኖዶሱና ዘጠነኛ ቀኑ


  • አባ አብርሃም የሀገረ ስብከቱን ጽ/ቤት ላለማስረከብ አስቂኝ መከራከሪያ አቀረቡ
  • ማኅበሯ ሌላው መንገድ ሁሉ አላስኬድ ሲላት አይመጥንም በሚል የሰንበት ማደራጃና መምሪያ ኃላፊነትን ከመምኅር እንቁባህሪ ላይ ለመንጠቅ የምታድረገው ሙከራ አልተሳካላትም።
  • ማኅበረ ቅዱሳንንየመፍረስ ስጋትን ጥሎበት የነበረው የማኅበራት መተዳደሪያ ደንብ እንደገና ውድቅ እንዲሆን እንቅልፍ አጥቶበት የነበረ ሲሆን እንደገና እንዲጠና ታዟል።   
አባ አብርሃም ርስት ጉልቴ ነው ያሉትን የሀገረ ስብከቱን ጽ/ቤት እንዲያስረክቡ የታዘዙትን ትዕዛዝ ለመቃመም ከተነሳው ጥያቄ ጋር የማይሄድ እኔ ከእርስዎ እሻላለሁ የሚል መከራከሪያ አቀረቡ። እኔ ምን አለኝ እና ነው መልስ የምባለው ሲሉ የነበሩት ሰው አሁን በራሴ ወጪ አጣሪ ተልኮ ከእኔ እና ከእርሰዎ ማን ጥሩ ስራ እንደሰራ ይጣራ? ሲሉ ጠይቀዋል። ይህም ጥያቄ አሜሪካ ለመመለስ ያላቸውን ከፍተኛ ጉጉት ያሳያል ተብሏል። ስውየውን የሚያስጨንቃቸው የቤተክርስቲያን ልጆች ባሉበት ቦታ ሁሉ ተገኝተው አባትነትን ማሳየት ሳይሆን ጥቅምና ምቾት ባለበት ቦታ ላይ መንቀባረር መሆኑንም አሜሪካ ለመመለስ ያላቸው ከፍተኛ ፍላጎት ያሳያል።
አሁን በቅርቡ እንኳ ወደ ሐረር ሀገረ ስብከት እንደ ደረሱ ለኔ የተመደበችው መኪና የትኛዋ ነች ብለው ሲጠይቁከእሳቸው በፊት ነበሩት አቡነ ዮሴፍ ይሄዱበት የነበረቸውን መኪና ሲያሳዩዋቸው ከት በለው ስቀው እኔ በዚህ መኪና ልሄድ? ብለው ጠይቀው ይህ መኪና ስለማይመጥነኝ በአስቸኳይ ከሞኤንኮ አዲስ መኪና ይገዛ ብለው አዲስ መኪና አስገዝተው በእስዋ መንፈላሰፍ ጀምረዋል። ድንቄም አባትነት።

Monday, May 21, 2012

ልሳነ ሌዋታን“ደጀ ሰላም” የማን ናት?

Click here to read in PDF
በዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል

አንብበው ይፍረዱ!


ይህ የሚመለከቱት መረጃ “ደጀ ሰላም” በመባል የሚታወቀውን ድረ-ገጽ/ብሎግ ሲጀመር ማኅበሩ የራሱ እንደሆነ በይፋ በድህረ ገጹ የገለጸበት/ያስተዋወቀበት በእንግሊዝኛ የድረ-ገጹ የመጀመሪያ የጽሑፉ “ሊንክ” ነበር። በተለይ deje-selam.blogspot.com/…/Ethiopia-mahberekidusan-eotc-past.html- የሚለውን ጽፈው ለመጎልጎል የሞከሩ እንደሆነ “ጭራሽ ከስፍራው ተነቅለዋል” የሚል መልስ ነው የሚያገኙ ለምን? ማኅበሩ ስራዬ ብሎ ቅድስት ቤተ-ክርስቲያንን መዋጋትና ማፈርስ ብሎም ቅድስት ቤተ-ክርስቲያንና የአባቶችን ክብር በሚነካ መልኩ ከአንድ በኢትዮጵያዊ ባህልና ወግ ያደገ ፍጡር በማይጠበቅ ልቅነትና ዋልጌነትን በእጅጉ አይለው በሚታዩበት ሁኔታ ማዋረድና ማንቋሸሽ እየተያያዛው ሲመጣ ጽሑፉን ከስፍራው በመንቀል የእኔ አይደለም እስከማለት ደርሰዋል። ቀደም ሲል ሌሎች የዜና ማእከላትና ድረ ገጾች ድረ ገጹን ዋቢ አድርገው ዘገባቸውን በሚያቀርቡበት ወቅት “ባለቤትነቱ ማህበረ ቅዱሳን የሆነውን ድረ ገጽ እንደዘገበው” እያሉ በዋቢነት ይጠቀሙበት የነበረውን ምክንያት ከዚህ የተነሳ ነበር። በዚህ ድረ ገጽ ስለ ቤተ-ክርስቲያን ያልተባለና ያልተነገረ እንዲሁም ያልተዋረደና ያልተዘለፈ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን የወንጌል አገልጋይ የለም።

ውድ አንባቢ! አሁን ብሎጉ የማን ነው? በሚለውን ነጥብ ላይ ከዚህ በላይ ብዙ ማለት እርስዎን ማሰላቸት ጊዜዎትንም ማባከን ነው የሚሆነው። ታድያ የቀረበውን መረጃ አንብቦ መረዳት የሚችል ሰው ሁሉ ድረ ገጹ የ“ማኅበረ ቅዱሳን” ለመሆኑ ይስተዋል የሚል እምነት የለኝም። ይህ ጽሑፍ ያስፈለገበትም ዋና ምክንያት አንዱ ሰሚም ሆነ ድረ ገጹን በዋቢነት የሚጠቀም ማንኛውም አካል ይህን እውነት አውቆ ይገባበት ዘንድ ለማሳሰብ ነው። እውነት ፈልገው ሲያበቁ እውነትን ከሚቀብሩ ደቂቀ ሌዋውያን ጋር እንደ መጎራበት ማለት ነው። ሌዋታን ማለት ቀንን የሚረግም ጠማማ የእባብ ዝርያ ነው።1954 እትምኢሳ.271, ኢዮብ 38 ይመልከቱ።

የድረ ገጽ ልዩ መታወቂያዎች

አንድ፥ ይህ ድረ ገጽ ገና ሲጀምር ራሱን ለማስታወቅ ያደረገው ጥረት ልብ ላለው እጅግ የሚያሳዝን ነው። ድረ ገጹ ራሱን ለማስተዋወቅ ከተጠቀመባቸው ስልቶቹ መከከል ሳይከሰስና ስሙ ሳይጠራ ሰለ ራሱ በራሱ እንደበት ክስ መስርቶ ለዳኝነት መጮኹ ነበር። የሀገሬ ሰው የአይጥ ምስክርዋ ድንቢጥ እንዲል በአንዳንድ ሚዛናዊነት በሚጎድልባቸው ሀገር ውስጥ የሚታተሙ የግል ጋዜጦችም ጭምር ከበሮ አስመትተዋል። ከዚህም የተነሳ ፍጹም መሰረት የሌላቸው ዜናዎቹና ዘገባዎችሁ የአንባቢያን ልብ ለመክፈል ችለዋል።
ሁለት፥ በዚህ ድረ ገጽ የሚሰራው ዜናም ሆነ የሚያቀርቡት ዘገባዎች የቤተ-ክርስቲያን ችግር ለመቅረፍና መፍትሔ ለማምጣት ሳይሆኑ ሆን  ተብሎ ወደ ከፋ ሁከትና ብጥብጥን የሚጋብዙ፣ ነገሮች አቅጣጫቻውን ስተው ሌላ ችግር እስኪ ፈጥሩ ደረስ የመለጠጥና የማጋነን ባሕርይ የተጸናወታቸው ያልተጻፈውን የቅጥፈት “ጸጋ” ባለ ቤቶችም ናቸው።

ሦስተኛ፥ የድረ ገጹ አዘጋጆችሁም ሆነ ደጋፊዎች የተገለጠ ማንነት ፍጹም በዘገባዎቻቸው የክርስትና ሥነ-ምግባር የማይታይባቸው፣ በዜናዎቻቸውም ኃላፊነትነትንና ተጠያቂነትን የማይሰማቸው፣ በአቀራረባቸው ፈሪሃ እግዚአብሔር የሌላቸው፣ እግዚአብሔር ያየናል ማለት ያልተቻላቸውም ናቸው። የጠሉት ሲቆርጡና ሲፈልጡ ለዓላማቸው መጠቀሚያ ጥሩ መሣሪያ የሆነ ሁሉ ደግሞ የሌለውን በመስጠትና በመለጠፍ በእውነት ላይ የሚያምጹና የጽድቅን መንገድ የሚያጨልሙ ናቸው። 

ድረ ገጽ አዘጋጆች የተጸናወታቸው አራት የውሽት ዓይነት/ልክፍቶች እንደሚከተለው ይመስላል

1ኛ. አሉባልተኞች ናቸው፥ አንድ ሰው አሉባልተኛ ነው ከተባለ በጥሬ ትርጉሙ አስመሳይ፣ ከሀዲ፣ የተናገረውን የማይደግም፣ አሉ ባይ ማለት ነው። ይኸውም በአንዱ ፊት ሌላ ተናግሮ ሲያበቃ ምራቁ ሳይደርቅ ደግሞ በሌላው ወገን ሰልፍ መሀከል ተገኝቶ የመጀመሪያውን ቃሉን ሽምጥጥ በማድረግ ጎራውን ለመምሰል በአዲስ መልክ ራሱን የሚገልጥ ሌላ የሚምስ የሚተነፍስ ማለት ነው። “ደጀ ሰላም” በመባል የሚታወቀው ድረ ገጽ አዘጋጆች ደግሞ በእንዲህ ዓይነቱ የአዋጊ ስልት “በእሳት” የተጠመቁ ነበልባሎች ናቸው። ርዕስ አስጩኸው ሲያበቁ ውስጡ ደግሞ ባዶ ቃላቶች ሰንገው የዋኁን ማህበረሰብ በማደናገር ረገድ ቁርጥ ነፍሰ ግዳዩ አባታቸው ዲያብሎስ! ይህ ብቻ አይደልም ይህ ማህበር የሚዘውራቸው ጋዜጦችና መጽሔቶች አጉል ተቆርቋሪነትን ሲያንጸባርቁ በዚህ ድረ ገጽ ደግሞ ቀንድ አውጥቶ ቤተ-ክርስቲያን መውጋትና ማፍረስ ነው የተያያዘው። በግርግር ተጠቃሚ ሌባ ነውና። ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ አሉባልተኞች የማይገባውን የሚናገሩ ለፍላፊዎችና በነገር ገቢዎች እንደሆኑ በ1ኛ ጢሞ 5፥13 በመግለጽ ማንም ከዚህ ዓይነቱ ልክፍት/በሽታ መራቅ እንደሚገባም አበክሮ ይመክራል።

2ኛ ቀዳዳዎች ናቸው፥ ይህ የውሸት ዓይነት ከሌሎቹ ይልቅ እጅግ የከፋ ነው። ቀዳዳ አይቋጥርም፣ ቀዳዳ ዕቃም ሆነ ምሥጢርን የማይጠብቅ ሰው ልብ አይጣልበትም። በቀዳዳ ዕቃ ነገርዎን ለማስቀመጥ ቢሞክሩ ለመቅለጥ ወስነዋል ማለት ነው። ይህ ዓይነቱ ባህሪ ወደ ድረ ገጹ አዘጋጆች ያመጠነው እንደሆነ በእጅጉ ተክነውበታል ማለቴ ሲያንሳቸው ነው። የድረ ገጹ አዘጋጆች ምንም ለቤተ-ክርስቲያን የቆምን ነን ከማለት ባይመለሱም ዘጋባዎቻቸው ሁሉ ግን የቤተ-ክርስቲያን አንድነትና የምእመናን ሰላም የሚያውኩና የሚነሱ ለመሆናቸው አሁን አሁን ደጀ ሰላም ስሙ በተነሳ ቁጥር እንደ እሬት እየከነከናቸው የመጡትን የደጋፊዎችሁ ምስክርነት ብቻ መስማት በቂ ነው። 

3ኛ ሸንጋዮች ናቸው፥ ይህ ማለት ቀለል ባለ አማርኛ በጥርሱ እየሳቀ በልቡ የሚራገም ማለት ነው። ጠቢቡ “ሽንገላን የምትናገር ከንፈር ጥፋት ታደርጋለች” እንዲል ከሸንጋዮች አንደበት ጥፋትን የሚጋብዝ ውዥንብርን የሚፈጥር እንጂ የምስራችን/መልካም ዜና አይሰማም። ሰበር ዜና ብሎ ታላላቆችን ሲዘልፍና ሲዘነጥል እንጂ “የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለችና ንስሃ ግቡ” አይልም። ሸንጋዮች በፊታችን መልካም መልካሙን አውርተውልን ሲያበቁ ዘወር ያልን እንደሆነ ደግሞ እግራችንን ተከትለው የሚቦጫጭቁን ናቸው። ደረ-ገጹም (ደጀ ሰላም) ሆነ ዋናው ማኅበሩ (“ማኅበረ-ቅዱሳን”) በዚህ ልክፍት ቀዳሚና ተከታይ የላቸውም። ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት በአጸደ ስጋ በህይወት ሳሉ ያለ ስማቸውን ስም እየሰጡ ያላሳረፍዋቸው ከሞቱ በኃላ የአዞ እንባ እያነቡ አጽማቸውን አፈርና ድንጋይ ለመነስነስና ለመወርወር ማንም አይቀድማቸውም ይህ ደግሞ እግዚአብሔር እጅግ ይጸየፈዋል።

4ኛ አጋናዮች ናቸው፥ አንድ ነገር እንዳለ እውነት በእውነቱ ማስፈር ማስቀመጥ አይሆንላቸውም። ያገኝዋትን ትንሽም እውነት ካላሰፍዋት፣ ካለጠጥዋትና እስክትበጠስ ድረስ ካልወጠርዋት ስራ የሰሩ ዜና የዘገቡም አይመስላቸውም። ታድያ ይህ ነውር የማያውቅ ወገን የተፋውን ትፋት ነው በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያንን በተመልከተ “ደጀ ሰላም” እንደዘገበችው እየተባለ የተሳሳተ መረጃ ለሕዝብ ጆሮ እየደረሰ ያለው።

ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል

United States of America

ማኅበረ ቅዱሳን ለተጻፈበት ደብዳቤ የሰጠው ምላሽ ሲገመገም

Click here to read in PDF
ሌባ እናት ልጇን አታምነውም ይባላል፡፡ ይህቺ እናት ልጇን ለማመን የተቸገረችው ልጁ የእጅ አመል ኖሮበት (እየሰረቀ) ያስቸገረ ሆኖ ሳይሆን እርሷ ያለባት ችግር ሁሉም ሰው እንዳለበት ሆኖ ሲለሚሰማት መሆኑ ግልጽ ነው፡፡
ማኅበረ ቅዱሳንም እንዲሁ እርሱ ሕገ ወጥነት በሙላት በውስጡ ስላለ ሌላው የሚያደርገው ነገር በሙሉ ሕጋዊ ያልሆነ መስሎ ይታየዋል፡፡ ለዚህ ጽሑፍ ምክንያት የሆነው ግንቦት 7/ 2004 . ማኅበሩ በድረ ገጹ ያለቀቀው መልእክት ነው፡፡ ይህ ጽሑፍ ገና ከርዕሱ በሕገ ወጦች በጨለማ የተዘጋጀው ደብዳቤ ተበተነ የሚለው ጽሁፍ በውስጡ የያዘውን ሐሳብ አለፍ አለፍ ብለን ስንመረምረው ሌባዋን እናትና አመኔታን ያጣውን ልጅ እንድናስታውስ ያደርገናል፡፡
ከጥቂት ቀናት በፊት ማኅበረ ቅዱሳን ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ማእከላዊ አስተዳደር ተገዥ ካለመሆን አልፎ የተቋሙን ሕልውና ወደ መፈታተን እንደ ደረሰ በማተት የሚከስ ደብዳቤ ለሕግ ተገዢ ባልሆኑ ግለሰቦች በጨለማ ተረቅቆ በመምሪያው ሓላፊ እንዲፈረም ተደርጎ ሊወጣ እንደ ነበር፤ ነገር ግን በመምሪያው ሓላፊው በቆሞስ መልአከ ጽዮን አባ ኅሩይ መታገዱን ገልጸን ነበር የሚለውን መግቢያው ያደረገው የማኅበሩ መልእክት ያለስሜ ስም ተሰጠኝ በሚል ብሶት ሮሮውን ለማስማት ጥረት እያደረገ ያለ አስመስሎታል፡፡

Sunday, May 20, 2012

የ“ኢሳት” የዜና ማእከል እና “የማህበረ ቅዱሳን ጊዜያዊ ጋብቻ!

Click here to read in PDF
ሙሉውን የጽሑፉን ይዘት ከማንበብዎ በፊት÷
1.     ጸሐፊው በጽሑፋቸው ውስጥ የጠቀሱትን የዜና ማዕከል “ማህበረ ቅዱሳን” በመባል ስለሚታወቀው መንፈሳዊ ካባ ያጠለቀ ጸረ ቤተ-ክርስቲያን ጸረ ሀገርና ጸረ ትውልድ ማኅበርን በተደጋጋሚ ሽፋን በመስጠት ጽድቁን በዜና መልክም ሆነ በሐተታ ተጠቃሹ የዜና ማዕከል ለአድማጮች ያቀረባቸውን ፍጹም ሚዛኑን የሳተና የተንጋደደ ዘገባን ብቻ በማስመልከት ያነጣጠረ ለመሆኑ÷ 
2.    አሁንም በጽሑፉ ውስጥ የተካተቱ ማናቸውም ሂሶችና ጥያቄዎች “ማህበረ ቅዱሳን” በማስመልከት እጃቸውን የጨመሩ የክፍሉ ሰራተኞች/ግለሰቦች/ እንጅ የመደብሩ ባለደረባዎችን በመላ የማያጠቃልል ለመሆኑ÷ 
3.    የጸሐፊው ዓላማም ሆነ የጽሑፉ ግብ በማጣመም ሌላ አንድምታ በመስጠትም “በኢሳት” የመጣ በዓይኔ ብሌን” በማለት አካኪ ዘራፍ የሚልም ስለማይታጣ  “ኢሳት” “ማህበረ ቅዱሳንን” በተመለከተም ሆነ “ደጀ-ሰላም” በመባል የሚታወቀውበኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያንና በተከታዮችዋ ላይ ሁከትን ለመፍጠር ታጥቆ የተነሳ የማህበሩ (“የማህበረ ቅዱሳን’) በአንድ ራስ ላይ ተደራቢ ምላስ/ልሳን ሆኖ የበቀለ ድረ ገጽ ዋቢ እያደረገ የሚዘግባቸው ዘገባዎችና የሚያቀርባቸው ማናቸውም ዓይነት ሀተታዎች ፍጹም ከእውነት የራቁና ነጭ ሐሰት መሆናቸው ብቻ ሳይሆን በወንጀል የሚያስጠይቅ ስራ እየሰራ ለመሆኑ÷ 
4.    በተጨማሪም “ኢሳት” ጭራሽ “የማህበረ ቅዱሳን” ልሳን አስኪያስመስልበት ድረስ እየሄደበት ያለውን አካሄድ ማለት ነፍሰ ገዳይን የመታደግ ስራ ትክክል አለመሆኑ ለማሳየት ምንም በማያሻማ ግልጽ በሆነ አማርኛ የቀረበ ጽሁፍ ለመሆኑ÷ 
5.    በመጨረሻም “ለኢሳት” ለብቻ ተብሎ የሚታለፍ እውነት አለመኖሩ እንደተጠበቀ ሆኖ ከአንደበት የሚወጣ ቃል የሰውን ልብ ከማሸፈት በላይ ህይወትም ይቀጫልና በተለይ የጉዳዩ ቀዳሚ ባለቤቶችና ሰላባዎች ሊሆኑ የሚችሉ/የምንችል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን እምነት ተከታዮችና ምእመን ሰላም ለመጠበቅ ሲባል ይህን ጽሑፍ ሊዘጋጅ ግድ ብለዋል። ደግሞም ሰው ይከበራል እንጅ ስጋ ለባሽ ሆኖ የሚፈራ፣ አምልኮም የሚገባው አንድ ስንኳ አለመኖሩን በሚያምን ልብ ተጻፈ። ጽሑፉ ልዩነትን የሚያሳይ እንጂ የክስ ደብዳቤም ሆነ የስሞታ ማመልከቻም አይደልም።
ከሰርጎ ገቦች የተነሳ በኢ/ኦ/ተ/ቤተ/ያን አስተዳደራዊ ማእከል ላይ ስለተፈጥረውና ስላለው ችግር በማስመልከት በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በስፋት ዜናዎችን በማቅረብና ሰፊ ሐተታዎችን በመስጠት ይታወቃል። ይህ መቀመጫውን ሆላንድ አምስተርዳም ያደረገ እንዲሁም በአሜሪካን ክፍለ ግዛት ዋሽንግተን ዲሲ በመሆን ከሚያሰራጫቸው ሀገራዊ ዜናዎች በብዙዎቻችን ዘንድ የታወቀ ለመሆኑ አልጠራጠርም። ስለ መረጃው ማእከል ከማንም የተለየ የጠለቀ ቅርበትም ሆነ ስለ ጣቢያው የተሻለ እውቀት ባይኖረኝም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ በሚኖረኝ የጊዜ ክፍተት አልፎ አልፎ አድማጭ ነኝ። የኢትዮጵያ ሕዝብ የአንድ ሃሳብ የበላይነት ከሚንጸባረቅበት ብቸኛ መንግስታዊ የዜና ማሰራጫ ተገላግሎ አማራጭ እድል በማግኘቱም ደስታዬ ወሰን የለውም። ታድያ ይህ መቀመጫውን በምእራቡ ዓለም ያደረገ “ኢሳት” በመባል የሚታወቀው የዜና ማእከል በብዙ የአገልግሎት ዘርፎቹ ሁሉንም የሚያስማማና ሁሉንም ያቀፈ ስራዎቹን ውሃ የሚቸልስ ስራዎችን ሲያቀርብ አንዴ፣ ሁለቴና በተደጋጋሚ መፈፀሙ በተለይ ለጉዳዩ ቅርበት ባላቸው የቅድስት ቤተ-ክርስቲያን ልጆችና ባለ አደራዎች ዓይን ሲታይ ነገሩ በቀላሉ የማይታለፍ ሆኖ በመገኘቱ ለመተራረምና እርስ በርስ ለመማማር ለማስታወሻም ያክል አንድ ማለቱ አስገዳጅ ሆኖ ተገኝቷል።

አህያቸውን ደጅ ያሳድሩና ጅብን ነገረኛ!

Click here in PDF
ምንጭ፡- ደጀ ብርሃን
ብዙዎቹ የማኅበረ ቅዱሳን ደጋፊዎች ድጋፋቸውን የሚገልጹት በሃይማኖታዊ እውቀት ላይ ተመስርተው ሳይሆን  ስሙን በቀባበት የቅዱሳን መጠሪያ ስር  ክርስቲያን በሚመስል ባህሪው  ካጠመዳቸው ሱስ የተነሳ ነው።
ማኅበረ ቅዱሳንን ለማወቅ ውልደቱንና እድገቱን መረዳት በጣም አስፈላጊው ነገር ነው። በዚያም ውስጥ የኖረበትን  ውስጠ ምስጢር ቀረብ ብሎ ማጥናትም በለበሰው ክርስቲያናዊ ካፖርቱ ስር ያለውን ማንነቱን ለመረዳት እጅግ አስፈላጊው ነገር ነው። ምክንያቱም  «መጽሐፍን በልባሱ፤ ሰውን በልብሱ አታድንቀው» የሚለውን ብሂል በመቀበል ገቢር ላይ አውለን ለማድነቅም ይሁን ለመንቀፍ የሚያስችል ሙሉ እውቀት እንዲኖረን ስለሚያስችለን ነው። ካገኘናቸው ጭብጦች ተነስተን ወደመንቀፉ ጥግ ስንደርስ በማኅበሩ ላይ የሚኖረውን አሉታዊ ምልከታ ከጭፍን ጥላቻና ምሬት የራቀ እንዲሆን ያደርገዋል። ስንደግፈውና ከፍ ከፍ ስናደርገውም ለመደገፍ የሚበቃን በጭብጥ ላይ የተመሰረተ እውቀታችን ከጭፍን ደጋፊነትና ከማኅበር አምላኪነት እንድንርቅ ያግዘናል። ስለዚህ የማኅበሩን አዎንታዊና አሉታዊ ማንነት በይፋ ለመናገር ምን ጊዜም በተሟላ መረዳት ላይ በተመሰረተ እውቀት መሆን እንዳለበት ለጥያቄ የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም። እኛን የሚነቅፉና የሚሳደቡ የማኅበሩ ደጋፊዎች እኛ ስለማኅበሩ ያለንን መረዳትና እውቀት ለማወቅ ከመፈለግ ይልቅ ለደጋፊነት ያበቃቸውን መረዳት በእኛ ላይ ለመጫን እጃቸውን ሲወራጩ ይስተዋላሉ። የማኅበሩ ደጋፊዎች እንደሚያዩን ሁሉ እኛም እነሱን የምናይበት ምልከታ ያለን ስለሆነ ልዩነቱ ከጭፍን ደጋፊነትና ከጭፍን ጥላቻ የወጣና የማኅበሩን ማንነት በማወቅ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ከሁለታችን ይጠበቃል።

የዮሀንስ ወልደ ነጎድጓድ ሰንበት ት/ቤት አመታዊ በዓል የዋልድባ አካባቢን ስኳር ፕሮጀክት በመቃመም እንደሚከበር ታወቀ

Click here to read in PDF
የዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ሰንበት ትምህርት ቤት የተመሰረተበትን 44ተኛ አመት ሲያከብር ዋነኛ አጀንዳዎቹ  መንግስት በዋልድባ አካባቢ ሊዘረጋ ያሰበውን የስኳር ፕሮጀክት መቃመምና ሲኖዶሱ ማኅበራትን አስመልክቶ የደረሰበትን ውሳኔ መቃወም መሆኑ ታወቀ። ሰንበት ት/ቤቱ ከማኅበረ ቅዱሳን 20ኛ ዓመት ጋር ተያይዞ በግንቦት 18 እና 19 ለማክበር የወሰነው ዓመታዊ በዓል ያሉት አጀንዳዎች ምን እንደሆነ አብዛኛው አባል የማያውቅ ሲሆን በውስጥ ግን በአመራር አካሉ የተያዘው አጀንዳ ከላይ የገለጽነው መሆኑ ተደርሶበታል። ይህም እንዲሆን ከፍተኛ ትግል እያደርጉ ያሉት ከቤተክርስቲያን ይልቅ በማኅበሩ አባልነታቸው ታምኖባቸው የሚሰጣቸውን ተልዕኮ በአግባቡ ይወጣሉ በሚባሉ የአመራር አካላት ናቸው። 

Saturday, May 19, 2012

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ 10 ጳጳሳትን ይዘው ወደ አክሱም ሄዱ

click here to read in PDF
  • መምህርን ዕንቆባሕርይ ከሰንበት ማደራጃ አይነሳም
  • የሚወገዝ ሰውም የለም
  • የደ/ር መስፍን ክህነት መሻር ይነሳልን ብለው ነበር  አልተሳከላቸውም
  • አባ አብርሃም የአሜሪካውን ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት እንዲያስረክቡ ታዘዋል
  • የማኅበረ ቅዱሳን ድረገጾች ውሸት እየፈበረኩ መዘገባቸውን ቀጥለዋልና የዘገቡትን ገልብጦ መረዳት ያስፈልጋል
ከሲኖዶስ ስብሰባ በስተጀርባ ሆኖ እንዳሻው ከሚጋልብባቸው ጳጳሳቱ ጋር የመከረውን ሁሉ ከስብሰባው መካሄድ ቀደም ብሎ የሲኖዶስ ውሳኔ አስመስሎ በማቅረብ ሕዝብን በተሳሳተ መረጃ ማደናገርና የተናገረው ሳይሆን ሲቀር ሊያፍር ሲገባው፣ ነገር ግን «ማፈር ደህና ሰንብት» ያለው ማኅበረ ቅዱሳን በድረገጾቹ ውሸት እየፈበረከና ምኞቱን የሲኖዶስ ውሳኔ አስመስሎ ማቅረቡን ቀጥሏል። ከሰሞኑ እንኳ እነእገሌ ዛሬ ይወገዛሉ አለ። ነገር ግን እንኳን ውግዘት እዚያ በሚያደርስ ሁኔታ የተደረገ ማጣራት አልተካሄደም። ማህበሩ በተሀድሶነት የከሰሳቸው ግለሰቦች ጉዳይ በተገቢው መንገድ ተጠንቶ ስላልቀረበና ግለሰቦቹም ተጠርተው ስላልተጠየቁና ምላሻቸው ስላልተሰማ፣ ጉዳዩ በዚህ የህግ አግባብ ተሰርቶ ወደፊት እንዲታይ የተባለውን፣ «ከዛሬ ጀምሮ በእያንዳንዱ የውሳኔ ሐሳብ ላይ በጥንቃቄ እየተወያየ እንደሚያጸድቀው ይጠበቃል።» ሲሉ ድረገጾቹ እንደተለመደው የልባቸውን ተምኔት ጽፈዋል። ይህ እንደማይሆን፣ ቅዱስነታቸው 10 ጳጳሳትን ይዘው ለቅዱስ ያሬድ በዓል ወደአክሱም ተጉዘዋልና፣ ዛሬ፣ እንኳን ይህ ፈጽሞ ያልተጣራና በጥቅምቱ ሲኖዶስ ስብሰባ ላይ በተወሰነበት ደረጃ የሚገኘው ጉዳይ ውሳኔ ሊያገኝ ቀርቶ የሲኖዶስ ስብሰባም እንደሌለ ለማወቅ ተችሏል።
ሌላው የማኅበሩ ምኞትና የሲኖዶስ ውሳኔ ተደርጎ የተዘገበው መምህር ዕንቆባሕርይ ከማደራጃ መምሪያ ሀላፊነታቸው እንዲነሱ ተወሰነ፤ አባ ህሩይም ወደሃላፊነታቸው እንዲመለሱ ሲኖዶሱ አዘዘ የሚለው ዘገባ ነው። ይህ ፈጽሞ ሊሆን የማይችል የማህበሪቱ ምኞት ነው። ማኅበሯ ቆሽቷ እርር ስላለ መምህር ዕንቆባሕርይን ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሃላፊነት ለማስነሳት በጳጳሳቶቿ በኩል ጥያቄ ብታነሣም፣ ኪራይ ሰብሳቢው አባ ኅሩይ ተመልሰው የሰንብት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሀላፊ እንደማይሆኑ፣ ማኅበሯ ተዋጠላትም አልተዋጠላትም መምህር ዕንቆባሕርይም እንደማይነሱና በመምሪያ ሀላፊነታቸው እንደሚቀጥሉ ተረጋግጧል።  
በማኅበራት ጉዳይ ላይ አጀንዳው እንደቀረበ ጳጳሳቱ ሁሉ መስማማታቸውን የገለጹ ሲሆን፣ «ጉዳዩ እኔን ለማፍረስ የተደረገ ነውና እንዴት እንዲህ ያለ ስምምነት አድርጋችሁ ትወጣላችሁ?» በማለት ጳጳሳቶቿን ከመጋረጃ በስተጀርባ ሰብስባ ጉዳዩን እንደገና እንዲያንገራግሩበት ለማድረግ ባደረገችው ጥረት ጳጳሳቶቿ በጉዳዩ ላይ አቧራ ለማስነሳት ሙከራ ያደረጉ ሲሆን በሁሉ ጥርስ ውስጥ የገባችውን ማኅበሯን ከመፍረስ ይታደጓታል ተብሎ አይታሰብም።
ማኅበሩ ከሲኖዶስ ስበሰባ በፊት በየድረገጾቹ አቡነ ጳውሎስን በግንቦቱ ሲኖዶስ ማውረድ አለብን የሚል ከፍተኛ ቅስቀሳ ሲያደርግ የነበረ መሆኑ ሲታወስ፣ ይህን ለማሳከትም በጥንተአብሶ ሰበብ ጳጳሳቶቿ ሙከራ እንዲያደርጉ ተልእኮ ሰጥታቸዋለች። ሌሎቹ ይህን ለማለት ባይደፍሩም፣ መቼም ያልተማረ ደፋር ነውና፣ ጨዋው (በትምህርት) አባ አብርሃም ቅባትነታቸውን፣ ኪራይ ሰብሳቢነታቸውን ሸፍነው ቅዱስነታቸውን «መናፍቅ» ለማለት መዳዳታቸው ብዙዎችን አስገርሟል። እርሳቸው ምን ያድርጉ አእምሮውአቸውን የተቆጣጠረችው ማኅበሯ በግንቦቱ ስብሰባ ላይ ከሌሎቹ በተለየ ሁኔታ የእርሷቸውን ተልእኮ እንደምትፈልገው አድርገው ለመፈጸም በመፋጠናቸው በትምህርት ሳይሆን፣ ፓትርያርክን በማንጓጠትና የማኅበሯን ተልእኮ ለመወጣት ከሌሎቹ ጳጳሳቶቿ ይልቅ አንደኛ ስለወጡ «ነደ ተሐድሶ» የሚል እንግዳ ማዕረግ ሰጥታዋለችና ለዚህ ይሆናል፤ ሽቅብ የተንጠራራው።
ሌላው ቄስ ነኝ ብሎ ሲዘላብድ የነበረው  መስፍን የተባለ ግለሰብ ክህነት ይመለስልኝ አቡነ ፋኑኤል ይገሰጹልኝ ብላ ማኅበርዋ ብትንደፋደፍም የአቡነ ፋኑኤል ስልጣንንና ክብር የሚጋፋ ምንም ነገር አልተፈጸመም። የመስፍን የክብር ቅስናም ሳይመለስለት ቀርቷል።
የአሜሪካ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤትን በተመለመተ ሲኖዶሱ የተነጋገረ መሆኑ ሲታወቅ አባ አብርሃም ከአንዲት ሴት ወ/ሮ ጋር የገዛሁት ቤት ነው? ምኑን ነው የምመልሰው ብለው ለመከራከርና በዚህም አቡነ ፋኑኤልን ለመስደብ ቢሞክሩም አቡነ ፋኑኤል ግን ለስድቡ መልስ ሳይሰጡ በሰከነ መንገድ ነገሩን ለማብራራት በመቻላቸው ሲኖዶሱ አባ አብርሃም ቤቱን እንዲመልሱ አዟል።

Friday, May 18, 2012

የአቡነ አብርሃም የጉድ ሙዳይ ሲከፈት

click here to read in PDF
አቡነ አብርሃምን የሚመለከት የጉድ ሙዳይ የሚል መጽሐፍ መጻፉን ባለፈው ጊዜ ገልጠን ነበር። የመጽሀፉ ሽፋንና ከፊል ታሪኩም እንደደረሰን እና በምቹ ጊዜ እንደምንለቀውም ተናግረናል። የመጽሐፉ ደራሲ ሲገለጽ በጊዜው ከልጅነት እስከ ዕውቀት ከእሳቸው ጋር ያደጉ ሰዎችን እንደሚያውቅ  እራሱም ስለእሳቸው በቂ እውቀት እንዳለው ያስረዳል። ያ ዳንኤል ክብረት የሚባል ሰው ልክ ያጣ ቅጥፈቱን በሀገር ልጅነትና በማኅበርተኛነት ስም ስለአስተጋባ እኛም የአገር ልጆቹ የምናውቀውን እውነት ለመናገራችን ማስረጃ እንዲሆነኝና ብዛታችንን እንዲያመለክትልን የጉድ ሙዳዩን አቡነ አብርሃምን እንደምናውቃቸው ብዬ በኔና በወዳጆቼ ስም ጽፌያለሁ ይለናል።
ዳንኤልንም "አንተም ታሪክህ የሚጻፍበት ቀን ስላለ ጠብቅ" የሚለው ሲገለጽ በጊዜው  ስለ አባ አብርሃም የሚያውቁትን ስጠይቅ እንቢኝ አልናገሩም ያሉ ወዳጆቼ የሚያውቁትን ሁሉ እንዲናገሩ ያደረጋቸው የአንተን ጽሁፍ ሳስነብባቸው ስለሆነ ለዚህ መጽሐፍ መጻፍ አንተም ቢሆን በዘባራቂነትህ ድርሻ አለህ። ይህን መጽሐፍ አንብበህም ምነው እጄ በተሰበረ ማለትህ አይቀርም ይለዋል። 
በትናንትናው ዕለት ቅዱስ ፓትርያርኩን ሃይማኖት እንዳለው ሰው "እርስዎንም በሃይማኖት ችግር እጠረጥርዎታለሁ" ብለው ሲናገሩ ትላልቆቹ ጳጳሳት እነ አቡነ ፊሊጶስ "እንዴት እንዲህ ይናገራሉ?" በማለት አባ አብርሃምን ገስጸው ተነስተው ጥለው በመውጣታቸው ክብራቸውን የማያውቁት ኣባ አብርሃም ተሸማቀው ቁጭ ማለታቸው ተሰምቷል።
 መቼም ጉድ ያለበት ሰው ንስሐ ገብቶ እስካልተመለሰ ድረስ ጉዱ እረፍት እየነሳ እወቁልኝ ንጹህ ነኝ ንጹህ ነኝ እያስባለ ያክለፈልፈዋልና? አባ አብርሃምን ሌላውን በመንቀፍ በመክሰስና ይወገዝልኝ በማለት ነውራቸውን ለመሸፈን ሌሎችንን ቆሻሻ በማለት የሚያደርጉት መሯሯጥ ስለበዛ አነሆ በሙላት ተዋወቋቸው ብለናል።