Saturday, May 10, 2014

ማኅበረ ቅዱሳን ቤተክርስቲያንን የማተራመስ ሥራውን በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረስብከትም ቀጥሏል።

ላለፉት 20 ዓመታት ቤተክርሰቲያንን እያተራመሰ እያመሰ እየበጠበጠ የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን ለማኅበሩ የማያሸረግዱ ብጹአን አባቶችን መቃወሙን እና ወጣቶችን ደግሞ ማሳደዱን አሁንም እንደቀጠለ ይገኛል። በተለይም በሄዱበት ሀገረ ስብከት ሁሉ ለማኅበረ ቅዱሳን ባለማንበርከክና ቤተክርስቲያንን በዱርዬ መንጋ እንዳትወረር ነቅተው በመጠበቅ የሚታወቁትን ብጹዕ አቡነ ሳዊሮስንም አላማቸው ገንዘብ በሆኑ አባላቱና ደጋፊዎቹ አማካኝነት መቃወሙን ቀጥሏል። ከአባላቱ መካከልም በተለይም  ሳሙኤል ደሪባ እና ጌታሁን አማረ የተባሉና ገንዘብ በማጭበርበርና ሙዳይ ምጽዋት በመገልበጥ የታወቁ ሁለት ግለሰቦች የሚያደርጉት የማበጣበጥ ሥራ ብዙ ቢሆንም የተፈለገውን ውጤት ግን ላስገኝላቸው አልቻለም።
ብጹዕ አቡነ ሳዊሮስ ከቅዱስ ፓትራርኩ ጋር
 ሳሙኤል ድሪባ ባካ ቅድስት ማርያም በምትባለው እና በወሊሶ ወረዳ ከምትገኘው ቤተክርስቲያን በሀገረ ስብከትም ሆነ በወረዳው ቤተክህነት ሳይታዘዝ ራሱ ሂሳብ ሹም መርጦ ገንዘብ ያዥ አስቀምጦ እና ቁጥጥር አድርጎ በሊቀ ጳጳሱ ከተፈቀደላቸው ኮሚቴዎች ውጭ በራሱ የሚታዘዝ ኮሚቴ በማን አለበኝነት በመፍጠር ከዘጠና ስምንት ሺህ ብር በላይ አጉድሏል። ይህም በኦዲተር ማስረጃ የተረጋገጠ ነው።

Saturday, March 15, 2014

ፍርድ ቤት ችሎት ላይ አይደለም የተቀመጠው “አሜን!” የማይለው፡፡

ከዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል
(መጋቤ ሐዲስ በጋሻው ወደ አውደ ምህረት ከተመለሰ በኃላ እርር ያሉት የማቅ ብሎጎች እሱን “መናፍቅ” ለማለት የሚያስችለን ነው ብለው ያመኑበትን ስድ ስድብ እየደረደሩ ይውጣልን ይጥፋልን የሚያሰኝ ዛር ነግሶባቸው እየተክለፈለፉ ይገኛሉ፡፡ መቸም ለዲያቢሎስ ጭንቀቱ የሚድነው መብዛቱ እና የሱ መንግስት ጠላቶች የመንግስቱን ሀሳብ ሲያፈርሱ ማየት ነው፡፡ ተከታዮቹም በጌታቸው መንግስት ላይ የተቃውሞ ሀሳብ ያለውን ክርስቲያን ሁሉ ማሳደድን እምቢኝ ብለው አያውቁም፡፡
ለማኅበረ ቅዱሳን መሪዎች የዲያቢሎስን አሰራር ለማፍረስ በተገለጠው የእግዚአብሔር ልጅ አምኖ የዲያቢሎስን አሰራር ለማፍረስ የሚንቀሳቀስ ክርስቲያን ሁሉ ጠላታቸው ነው፡፡ ለዚህ ነው ሰሞኑን በሁሉም ብሎጎቻቸው እንደገና መጋቤ ሐዲስ በጋሻው ላይ መዝመት የጀመሩት፡፡ የወላይታ ሶዶው ጉባኤ እንዳይካሄድ ያደረጉት ጥረት ሁሉ  ከሽፎ ጉባኤው ከፍተኛ ህዝብ በተገኘበት መካሄዱ ቢያቃጥላቸው “ስህተት” ብለው ያገኙትን ነገር ነቅሰው አወጡ፡፡ ታዲያ በማቅ መመዘኛ ትልቁ ምንፍቅና በ10 ደቂቃ 20 ጊዜ አሜን ማለት ሆኖ ተገኘ፡፡ ከታወሩ አይቀር እንዲህ ነው እንጂ!!!
ሙሉጌታ ወልደ ገብርኤል አሜን ለምን ይባላል አሜን ማለት የሊቅነት ማነስ ውጤት ነው የሚለውን የአንድ አድርገን ዘገባ እንዲህ ይተቻል፡፡ መልካም ንባብ!! )
ነዋሪነታቸው ጀርመን ፍራንክፈርት  የሆነ አንድ በአካባቢው የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታይ ምእመን ባሳለፍነው ሳምንት በኢሜይል አድራሻዬ “ … እርስዎስ ምን ይላሉ?” ሲሉ ነበር የጠየቁኝ። አያይዘው ከላኩልኝ ሊንክ በተጨማሪ ለይተው አውጥተው አስተያየቴን የጠየቁበት ጽሑፍ እንደሚከተለው ይነበባል።
ሊቃውንቱ ሲሰብኩ ሰው ወደ ውስጡ እንዲመለከትና በጥሞና እና በአስተውሎ የእግዚአብሔር ቃል እንዲያደምጥ ሲያደርጉ ነበር እኛ የምናውቀው፤ አሁን አሁን በአስር ደቂቃ ጊዜ ውስጥ 20 ጊዜ በላይ ‹‹አሜን›› የሚያስብለውን ሆነ ‹‹አሜን›› በማያስብለው ምዕመኑን ጮኻሂ የማድረግ አዝማሚያ እየታየ ነው፤ መናፍቃን ቤት የሚገኝው ጩኽት እኛ ቤትም ለመግባት ደጃፍ ላይ እያኮበኮበ ይገኛል፡፡[http://www.andadirgen.org/2014/02/blog-ost_5495.html]
እኚህ ወንድም አያይዘው በላክሉኝ መልዕክት የእግዚአብሔር መንጋ ለመበተን የሌሊት እንቅልፍ የማያውቀው ራሱንማኅበረ ቅዱሳንበማለት በሚጠራው ቡድን የሚዘወርአንድ አድርገንየተባለ መካነ ድር ነበርና ከዚህ የሽፍታ ድረ ገጽ ያነበቡትን ጽሑፍ ተንተርሰው የተፈጠረባቸው ጥያቄ ሲጨመቅ ፍሬ ነገሩ እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ።
የመጀመሪያ ጥያቄአቸው በደረቁ በስብከት ጊዜ አሜን ማለት ይቻላል አይቻልም?” አክሎውም የሚቻል ከሆነስ በአንድ ስብከት ውስጥ ስንት ጊዜ ነው አሜን ማለት የሚቻለው?” ባነበቡት እንግዳ ትምህርት የተደናገጡ ስለሆነም ለመሆኑ አሜን ማለት ምን ማለት ነው? አሜን የአማርኛ/የግዕዝ ቋንቋ ነው ወይስ ከሌላ ቋንቋ የተገኘ ቃል?” በማለት በአሜን “… ዙሪያ መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረውን ትምህርት ያካፍሉን ዘንድ በትህትና እጠይቃለሁ። እግዚአብሔር አገልግሎትዎን ይባርክ።ስም አለው።!

Wednesday, February 19, 2014

ቋሚ ሲኖዶሱ መጋቢ ሐዲስ በጋሻው አገልግሎቱን እንዲቀጥል ፈቀደ


በማህበረ ቅዱሳን ውል አልባ ክስ አገልግሎቱን አቋርጦ የነበረው መጋቤ ሐዲስ በጋሻው አገልግሎቱን እንዲቀጥል ተፈቀደ። ማኅበረ ቅዱሳን በአንካሳ ልቡ እያነከሰ ወንድሞችን ከቤተክርስቲያን ጠራርጎ የማስወጣት ዘመቻው አካል የሆነው የበጋሻው ክስ አቅሙ የሰለለ እና የምንፍቅናን ምንነት ያላገነዘበ መሆኑ ታውቆ አገልግሎቱ እንዲቀጥል መደረጉ ለእውነተኛ ኦርቶዶክሳውያን ሁሉ ትልቅ ድል ነው።
አሁንም ማኅበሩ ይህን እፍረቱን ተመለክቶ ወንድሞችን ማሰደዱን መክሰሱን ትቶ በእውነት ለቤተክርስቲያን የሚጠቅማትን ነገር ብቻ ላይ ቢያተኩር ይገባዋል እንላለን።
አሊያ የእውነተኛው ከሳሽ እና የሀሰት አባት የሆነው የዲያቢሎስ ደቀ መዝሙር እንደሆነ ይቀጥላል።

Thursday, January 23, 2014

ማኅበረ ቅዱሳን በአዲሱ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መዋቅራዊ ለውጥ ምክንያት እየደረሰበት ያለው ተቋሞ ተጋግሎ ቀጥሏል፡፡

REadin PDF:

በየሆቴሉ በድብቅ ይሰበሰባሉ ሲባሉ የቆዩት የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አለቆች በገሀድ በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ ተሰብስበው ፓትርያርኩንና አንዳንድ የማኅበሩን ደጋፊ ሊቃነ ጳጳሳት አስጠነቀቁ፡፡ ጥያቄዎቻችን ምላሽ የማያገኙ ከሆነ የቤተክርስቲያኒቱ አስተዳደር በጥቁር ራስ (መነኮሳት ባልሆኑ) ሰዎች እንዲካሄድ በሕጋዊ መልኩ እንደሚጠይቁ አስረድተዋል፡፡
የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት ሰራተኞች ቤተክርስቲያኒቱ የአሰራር ለውጥ እንደሚያስፈልጋት አምነው ለውጡ ሁለንተናዊና መላውን የቤተክህነቱ ክፍል ሊያቅፍ እንደሚገባ ሕጉም ከዋናው ከሕገ ቤተክርስቲያን መጀመር እንዳለበትና በየደረጃው ደንቦችና መመሪያዎች ሊወጡ እንደሚገባው አስረድተው ይህንን የሚሰራው አካልም ከቅዱስ ሲኖዶስ፣ ከሊቃውንት ጉባዔ፣ በየደረጃው ከሚገኙ የቤተክርስቲያኒቱ መዋቅር ሰራተኞች ፣ ከገለልተኛ ባለሙያዎች ምእመናንና የሰንበት ት/ቤት ተወካዮች በተወጣጣ ኮሚቴ መሰራት እንደሚገባው አስምረውበታል፡፡
ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ጥያቄያችሁ በቀላሉ የሚታይ አይደለም ትኩረት ይፈልጋል  በማለት ኮሚቴ እንዲቋቋም ፈቅደዋል በቤተክህነቱ አዳራሽ መሰብሰብ እንደሚችሉ አረጋግጠውላቸዋል፡፡
ስብሰባው ያበሳጫቸው አቡነ እስጢፋኖስ ግለቱ ከብዷቸው ወደ አሜሪካ እንደሚሄዱ ተናግረዋል፡፡

Friday, January 17, 2014

የአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በህዳር 12 ከተሰበሰበ ገንዘብ ከሁለት መቶ ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ተመዘበረ፡፡

በደብረምሕረት ቅዱስ ሚካኤል የደብሩ አስተዳዳሪ የዓመት ፍቃድ በመሆናቸው በቆጠራው ላይ ስላልተገኙ ይህንንም እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠርና የሰበካ ጉባዔ ምክትል ሊቀ መንበር ስልክ ተደውሎላቸው ቆጠራውን አቋርጠው በመውጣታቸው የደብሩ ዋና ጸሐፊ መ/ስ አብርሃም አቧይ  የወረዳው ስራ አስኪያጅ የአባ አእምሮ የቅርብ ዘመድ ከወረዳ የተወከሉት ወ/ሮ አባይ እና የሀገረ ስብከቱ ጸሐፊ ወ/ሮ አዲስ ዓለም እንዲሁም በአዲስ አበባ ሙስናና ዘረፋን በማበረታታት እነ የካ ሚካኤልን እንዳያገግሙ አድርጎ በዘረፋ ባዶ ያስቀራቸው በአዲስ አበባ ከተማ ለተለያዩ የውጪ ሀገር ኗሪዎች 7 ፎቅ ቤቶችን በተለያዩ አካባቢዎች  ሰርቶ የሚያከራየው ቀድሞ አለቃ የአደራው ንጉሤ ሴት ልጅ  ወ/ት እጸገነት አደራው በገንዘብ ያዥነት እንዲሁም በካቴድራሉ መልካም ሰው በመምሰል ለሁሉ ወዳጅ የሆነው አቶ ፋንታሁን ምረቴ እና ሊቀ ትጉሃን ኃ/ጊዮርጊስ በጋራ ዘረፋውን ማከናወናቸው ታውቋል፡፡

Friday, October 18, 2013

ይድረስ ለአቶ ተመስገን ደሳለኝ፡ ፋክት ወይስ ፕሮፖጋንዳ?

በቅድምያ “ቀጣዩ የኢሕአዴግ ዒላማ ማኅበረ ቅዱሳን ይኾን?” [ፋክት መጽሔት፤ ቁጥር 14 መስከረም 2006 ዓ.ም] ሲሉ ባልዋሉበት አልያም በሽፍጥነት የሐሰት ምስክርነታቸውን ለሰጡ/ለጻፉ ግለሰብ ራሴን ላስተዋውቅ። ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል እባላለሁ። ከልጅነት እስከ እውቀት ያደግኩት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ነው። ራሱን “ማኅበረ ቅዱሳን” እያለ የሚጠራ መንፈሳዊ መልክ ያለው መሰሪ – ጸረ ሀገር፣ ጸረ ትውልድና ጸረ ቤተ ክርስቲያን ቡድን ተገንዞ ከተቀበረበት መቃብር ቀስቅሰው ሊነግሩን እንደቃጣዎት ዓይነት ሳይሆን “ማህበረ ቅዱሳን” ማለት ሰይጣን ራሱ በቁሙ የሚመለክበት፣ የሚዘከርበትና የሚታሰብበት የሲዖል ተረፈ ምርት ለመሆኑ በህይወቴ የማውቀው ሰው ነኝ። ሕገ መንግሥታዊ የመማር መብቴ ተጥሶ ለዓመታት ከለፋሁበት የትምህርት ገበታዬ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ ያለ ስሜ ስም ተለጥፎብኝ እንድባረር የተደረግኩ፣ ከአንድም ሁለቴ በአንድ የክስ መዝገብ ለከፍተኛ እንግልትና ለእስር የተዳረግኩ፣ በሞትና በህይወት መካከል የተገረፍኩና በመጨረሻም አገሬን ለቅቄ በስደት ምድር በኬንያ ለሁለት ዓመት ከአምስት ወር ያለ ምንም የህይወት ዋስትንና እርዳታ የተንገላታሁ የሰው ሚስት ሳማግጥ ተገኝቼ ይመስሎታል? ከነተረቱ “ያልተነካ ግልግል ያውቃል” ነው የሚባለው። ለመሆኑ እርስዎ ስለ “ማኅበረ ቅዱሳን” ያልሆነውን ነው! በማለት ይህን ያህል ለማለት የደፈሩ እንደ አንድ የማኅበሩ አባል በጋዜጠኝነት ስም የአባልነት ግዴታዎ መወጣትዎ ነው ወይስ ነኝ እንደሚሉት “በጋዜጠኝነትዎ” ነው? ቁምነገሩ ያለው ወዲህ ነው። “ቀጣዩ የኢሕአዴግ ዒላማ ማኅበረ ቅዱሳን ይኾን?” ሲሉ በጻፉት ጽሑፍ በጋዜጠኝነትዎ እንዳልነቅፎት፥ በኢትዮጵያ ውስጥ ወንጀል ሰርተው ያለ ተጠያቂነት ለመኖር ይሻሉ? 
እንግዲያውስ በጋዜጠኝነት የሥራ መስክ ይሰማሩ።

Thursday, October 17, 2013

ማኅበረ ቅዱሳን በአጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ስብሰባ ላይ በደረሰበት ተቃውሞ ተወካዮቹ ስብሰባ ረግጠው ወጡ

ምንጭ- አባ ሰላማ
32ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባ ፓትርያርኩን ጨምሮ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተክህነት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ ከየሀገረ ስብከቱ የተወከሉ የአህጉረ ስብከቶች ሥራ አስኪያጆች፣ ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎችም በተገኙበት ጥቅምት 3/2006 ዓ.ም ተጀምሯል፡፡ በስብሰባው ላይ ከየአህጉረ ስብከቶች በመጡ ሥራ አስኪያጆች የሥራ ሪፖርት እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን ውይይትም እየተደረገ ነው፡፡

 በስብሰባው የመጀመሪያ ቀን በጠቅላይ ቤተ ክህነት የካህናት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ሊቀ ካህናት ኃይለ ስላሴ ዘማርያም ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን ምን ያህል አስጊ ኃይል እንደ ሆነና ከተለያዩ የንግድ ተቋማቱ የሚሰበስበውንና በቤተክርስቲያን ስም ከአገር ውስጥና ከውጭ የሚሰበስበውን ገንዘብም ኦዲት እንደማይደረግ የገለጹ ሲሆን፣ በዚህም ማቅ ኪራይ ሰብሳቢ ድርጅት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

 በትናንትናው ዕለት ደግሞ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ – ወሊሶ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ የሆኑት መልአከ ገነት አባ አፈወርቅ ዮሐንስ በሀገረ ስብከታቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በዓመቱ ከገጠሟት ችግሮች መካከል ዋና አድርገው የጠቀሱት ማኅበረ ቅዱሳንን ሲሆን፣ ማኅበሩ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጪ ቤተ ክርስቲያኗ የራሷ መተዳደሪያ ቃለ አዋዲ እያላት ቃለ ዐዋዲውን አሻሽሎ ሌላ መተዳደሪያ በማውጣትና የቤተክርስቲያንን መዋቅር በማዳከምሕዝበ ክርስቲያኑ ፐርሰንት እንዳይከፍሉና ሕዝቡ ለማኅበሩ በአባልነት ተመዝግቦ ለማኅበሩ እንዲከፍል በመቀስቀስ በቤተ ክርስቲያን ላይ ደባ መፈጸሙን ጠቁመዋል፡፡ በተጨማሪም የሀገረ ስብከቱ የሆነውን ሱቅ እንደማንኛውም ምእመን ተከራይተው ኪራይ አንከፍልም በማለት ማመጻቸውንና ሕዝብን ማነሳሳታቸውን ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ማኅበሩ እንደ ትልቅ ስልት የያዘው የሕዝብ ተመራጭ በመምሰል በሰበካ ጉባኤ፣ በሰንበት ትምህርት ቤቶች በልማትኮሚቴና በስብከተወንጌል ኮሚቴነት በመግባት የበላይ መመሪያን አለመቀበልንና መዋቅር ማዳከምን ነው ብለዋል፡፡ ለማሳያነትም በወንጪ፣ በወሊሶ፣ በሰበታ አዋስ ወረዳ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሕዝብን የመከፋፈልና የማሳመፅ ድርጊት በመፈጸም ላይ መሆናቸውን በማስረጃ አስደግፈው አጋልጠዋል፡፡ ከዚህም ሌላ በ11ዱ ወረዳዎች ኔትዎርክ በመዘርጋት የራሳቸውን ሥራ በመተው በሀገረ ስብከቱ ላይ ሰዎችን በማደራጀት ላይ እንደሚገኙ በማስረዳት ቅዱስ ሲኖዶስ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡

Thursday, September 26, 2013

ከሰማይ ወረደ በተባለው መስቀል ላይ ሳይንሳዊ ምርመራ ማድረግ ክልክል ነው ተባለ

ነገሩ “በሃይማኖት ጉዳይ ሳይንስ ጣልቃ አይገባም” የሚል ቃና ያለው ይመስላል

ከሰሞኑ ከሰማይ ወረደ ስለተባለው መስቀል ከዘገቡት የፕሬስ ውጤቶች መካከል አንዱ የሆነው አዲስ አድማስ ጋዜጣ በመስከረም 11/2006 ዓ.ም. እትሙ ላይ “ከሰማይ ወረደ ለተባለው መስቀል የሳይንስ ምርመራ አይፈቀድም ተባለ” የሚል ርእስ ይዞ በድጋሚ ወጣ፡፡ ጋዜጣው እንደ ዘገበው መስቀሉ ከሰማይ ወርዷል ለሚለው የብዙዎች ጥርጣሬ ማረጋገጫ መስጠት እንዲቻል “ወረደ” በተባለው መስቀል ሳይ ሳይንሳዊ ምርመራ ይደረግ ዘንድ ስለመጠየቁ ሐሳብ ቀርቦ እንደሆን የተጠይቁት፣ መልስ የሠጡትና የዚህ “ተአምር ብቸኛ የዓይን ምስክር የሆኑት” መጋቤ ሐዲስ ፍስሃ እስካሁን “ከሰማይ የወረደውን መስቀል” አድናቂዎች እንጂ ምርምር እናካሂድ የሚል ጥያቄ ያቀረቡ ምሁራን አለመኖራቸውን ጠቅሰው ጥያቄውን የሚያቀርቡ ቢኖሩ ግን “የማይሞከር ነው” ሲሉ ተከላክለዋል፡፡


ይህ “ተአምር” ለሳይንሳዊ ምርምር ክፍት እንዳይሆን መከልከሉ ሰዎች በጉዳዩ ላይ ከፊት ይልቅ እንዲጠራጠሩ ሰፊ በር የሚከፍት መሆኑ እሙን ነው፡፡ ይሁን እንጂ “ያደረገችውን ታስታውቅ ከወደ ደረቷ ትታጠቅ” እንዲሉ መጋቤ ሐዲስ ፍስሀ ያደረጉትንና የሆነውን ስለሚያውቁ “የማይሞከር ነው” በሚል “በሃይማኖት ጉዳይ ሳይንስ ጣልቃ አይገባም” አይነት መከራከሪያ አቅርበው ለምርምር በሩ ዝግ መሆኑን ፈርጠም ብለው ተናግረዋል፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ “ወረደ” የተባለውን መስቀል ሳይንስ ቢያረጋግጠው ከሰማይ የወረደ እስከሆነ ድረስ ምንም የሚያስፈራ ነገር አይኖርም ነበር፡፡ ነገር ግን አስቀድመን በእርግጠኛነት እንደተናገርነው መስቀሉ ከምድር የተገኘ ስለሆነ “ከቶም አይሞከርም” ብለው “የነገርኳችሁን ማመን እንጂ መመርመር አትችሉም” የሚል መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ ይህ ግን ትክክል አይደለም፡፡