Friday, October 18, 2013

ይድረስ ለአቶ ተመስገን ደሳለኝ፡ ፋክት ወይስ ፕሮፖጋንዳ?

በቅድምያ “ቀጣዩ የኢሕአዴግ ዒላማ ማኅበረ ቅዱሳን ይኾን?” [ፋክት መጽሔት፤ ቁጥር 14 መስከረም 2006 ዓ.ም] ሲሉ ባልዋሉበት አልያም በሽፍጥነት የሐሰት ምስክርነታቸውን ለሰጡ/ለጻፉ ግለሰብ ራሴን ላስተዋውቅ። ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል እባላለሁ። ከልጅነት እስከ እውቀት ያደግኩት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ነው። ራሱን “ማኅበረ ቅዱሳን” እያለ የሚጠራ መንፈሳዊ መልክ ያለው መሰሪ – ጸረ ሀገር፣ ጸረ ትውልድና ጸረ ቤተ ክርስቲያን ቡድን ተገንዞ ከተቀበረበት መቃብር ቀስቅሰው ሊነግሩን እንደቃጣዎት ዓይነት ሳይሆን “ማህበረ ቅዱሳን” ማለት ሰይጣን ራሱ በቁሙ የሚመለክበት፣ የሚዘከርበትና የሚታሰብበት የሲዖል ተረፈ ምርት ለመሆኑ በህይወቴ የማውቀው ሰው ነኝ። ሕገ መንግሥታዊ የመማር መብቴ ተጥሶ ለዓመታት ከለፋሁበት የትምህርት ገበታዬ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ ያለ ስሜ ስም ተለጥፎብኝ እንድባረር የተደረግኩ፣ ከአንድም ሁለቴ በአንድ የክስ መዝገብ ለከፍተኛ እንግልትና ለእስር የተዳረግኩ፣ በሞትና በህይወት መካከል የተገረፍኩና በመጨረሻም አገሬን ለቅቄ በስደት ምድር በኬንያ ለሁለት ዓመት ከአምስት ወር ያለ ምንም የህይወት ዋስትንና እርዳታ የተንገላታሁ የሰው ሚስት ሳማግጥ ተገኝቼ ይመስሎታል? ከነተረቱ “ያልተነካ ግልግል ያውቃል” ነው የሚባለው። ለመሆኑ እርስዎ ስለ “ማኅበረ ቅዱሳን” ያልሆነውን ነው! በማለት ይህን ያህል ለማለት የደፈሩ እንደ አንድ የማኅበሩ አባል በጋዜጠኝነት ስም የአባልነት ግዴታዎ መወጣትዎ ነው ወይስ ነኝ እንደሚሉት “በጋዜጠኝነትዎ” ነው? ቁምነገሩ ያለው ወዲህ ነው። “ቀጣዩ የኢሕአዴግ ዒላማ ማኅበረ ቅዱሳን ይኾን?” ሲሉ በጻፉት ጽሑፍ በጋዜጠኝነትዎ እንዳልነቅፎት፥ በኢትዮጵያ ውስጥ ወንጀል ሰርተው ያለ ተጠያቂነት ለመኖር ይሻሉ? 
እንግዲያውስ በጋዜጠኝነት የሥራ መስክ ይሰማሩ።

Thursday, October 17, 2013

ማኅበረ ቅዱሳን በአጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ስብሰባ ላይ በደረሰበት ተቃውሞ ተወካዮቹ ስብሰባ ረግጠው ወጡ

ምንጭ- አባ ሰላማ
32ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባ ፓትርያርኩን ጨምሮ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተክህነት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ ከየሀገረ ስብከቱ የተወከሉ የአህጉረ ስብከቶች ሥራ አስኪያጆች፣ ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎችም በተገኙበት ጥቅምት 3/2006 ዓ.ም ተጀምሯል፡፡ በስብሰባው ላይ ከየአህጉረ ስብከቶች በመጡ ሥራ አስኪያጆች የሥራ ሪፖርት እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን ውይይትም እየተደረገ ነው፡፡

 በስብሰባው የመጀመሪያ ቀን በጠቅላይ ቤተ ክህነት የካህናት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ሊቀ ካህናት ኃይለ ስላሴ ዘማርያም ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን ምን ያህል አስጊ ኃይል እንደ ሆነና ከተለያዩ የንግድ ተቋማቱ የሚሰበስበውንና በቤተክርስቲያን ስም ከአገር ውስጥና ከውጭ የሚሰበስበውን ገንዘብም ኦዲት እንደማይደረግ የገለጹ ሲሆን፣ በዚህም ማቅ ኪራይ ሰብሳቢ ድርጅት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

 በትናንትናው ዕለት ደግሞ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ – ወሊሶ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ የሆኑት መልአከ ገነት አባ አፈወርቅ ዮሐንስ በሀገረ ስብከታቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በዓመቱ ከገጠሟት ችግሮች መካከል ዋና አድርገው የጠቀሱት ማኅበረ ቅዱሳንን ሲሆን፣ ማኅበሩ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጪ ቤተ ክርስቲያኗ የራሷ መተዳደሪያ ቃለ አዋዲ እያላት ቃለ ዐዋዲውን አሻሽሎ ሌላ መተዳደሪያ በማውጣትና የቤተክርስቲያንን መዋቅር በማዳከምሕዝበ ክርስቲያኑ ፐርሰንት እንዳይከፍሉና ሕዝቡ ለማኅበሩ በአባልነት ተመዝግቦ ለማኅበሩ እንዲከፍል በመቀስቀስ በቤተ ክርስቲያን ላይ ደባ መፈጸሙን ጠቁመዋል፡፡ በተጨማሪም የሀገረ ስብከቱ የሆነውን ሱቅ እንደማንኛውም ምእመን ተከራይተው ኪራይ አንከፍልም በማለት ማመጻቸውንና ሕዝብን ማነሳሳታቸውን ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ማኅበሩ እንደ ትልቅ ስልት የያዘው የሕዝብ ተመራጭ በመምሰል በሰበካ ጉባኤ፣ በሰንበት ትምህርት ቤቶች በልማትኮሚቴና በስብከተወንጌል ኮሚቴነት በመግባት የበላይ መመሪያን አለመቀበልንና መዋቅር ማዳከምን ነው ብለዋል፡፡ ለማሳያነትም በወንጪ፣ በወሊሶ፣ በሰበታ አዋስ ወረዳ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሕዝብን የመከፋፈልና የማሳመፅ ድርጊት በመፈጸም ላይ መሆናቸውን በማስረጃ አስደግፈው አጋልጠዋል፡፡ ከዚህም ሌላ በ11ዱ ወረዳዎች ኔትዎርክ በመዘርጋት የራሳቸውን ሥራ በመተው በሀገረ ስብከቱ ላይ ሰዎችን በማደራጀት ላይ እንደሚገኙ በማስረዳት ቅዱስ ሲኖዶስ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡

Thursday, September 26, 2013

ከሰማይ ወረደ በተባለው መስቀል ላይ ሳይንሳዊ ምርመራ ማድረግ ክልክል ነው ተባለ

ነገሩ “በሃይማኖት ጉዳይ ሳይንስ ጣልቃ አይገባም” የሚል ቃና ያለው ይመስላል

ከሰሞኑ ከሰማይ ወረደ ስለተባለው መስቀል ከዘገቡት የፕሬስ ውጤቶች መካከል አንዱ የሆነው አዲስ አድማስ ጋዜጣ በመስከረም 11/2006 ዓ.ም. እትሙ ላይ “ከሰማይ ወረደ ለተባለው መስቀል የሳይንስ ምርመራ አይፈቀድም ተባለ” የሚል ርእስ ይዞ በድጋሚ ወጣ፡፡ ጋዜጣው እንደ ዘገበው መስቀሉ ከሰማይ ወርዷል ለሚለው የብዙዎች ጥርጣሬ ማረጋገጫ መስጠት እንዲቻል “ወረደ” በተባለው መስቀል ሳይ ሳይንሳዊ ምርመራ ይደረግ ዘንድ ስለመጠየቁ ሐሳብ ቀርቦ እንደሆን የተጠይቁት፣ መልስ የሠጡትና የዚህ “ተአምር ብቸኛ የዓይን ምስክር የሆኑት” መጋቤ ሐዲስ ፍስሃ እስካሁን “ከሰማይ የወረደውን መስቀል” አድናቂዎች እንጂ ምርምር እናካሂድ የሚል ጥያቄ ያቀረቡ ምሁራን አለመኖራቸውን ጠቅሰው ጥያቄውን የሚያቀርቡ ቢኖሩ ግን “የማይሞከር ነው” ሲሉ ተከላክለዋል፡፡


ይህ “ተአምር” ለሳይንሳዊ ምርምር ክፍት እንዳይሆን መከልከሉ ሰዎች በጉዳዩ ላይ ከፊት ይልቅ እንዲጠራጠሩ ሰፊ በር የሚከፍት መሆኑ እሙን ነው፡፡ ይሁን እንጂ “ያደረገችውን ታስታውቅ ከወደ ደረቷ ትታጠቅ” እንዲሉ መጋቤ ሐዲስ ፍስሀ ያደረጉትንና የሆነውን ስለሚያውቁ “የማይሞከር ነው” በሚል “በሃይማኖት ጉዳይ ሳይንስ ጣልቃ አይገባም” አይነት መከራከሪያ አቅርበው ለምርምር በሩ ዝግ መሆኑን ፈርጠም ብለው ተናግረዋል፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ “ወረደ” የተባለውን መስቀል ሳይንስ ቢያረጋግጠው ከሰማይ የወረደ እስከሆነ ድረስ ምንም የሚያስፈራ ነገር አይኖርም ነበር፡፡ ነገር ግን አስቀድመን በእርግጠኛነት እንደተናገርነው መስቀሉ ከምድር የተገኘ ስለሆነ “ከቶም አይሞከርም” ብለው “የነገርኳችሁን ማመን እንጂ መመርመር አትችሉም” የሚል መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ ይህ ግን ትክክል አይደለም፡፡

Monday, August 5, 2013

በእጅ አዙር የቤተክርስቲያኒቱን መዋቅር መቆጣጠር የሚፈልገዉ የጸሐፍት ፈሪሳዊያን ጥርቅሙ ማህበረ ቅዱሳን በአሰበ ተፈሪ ድብቅ ሴራዉ ተጋለጠ

Read In PDF: Asebeteferi
 ከመሪጌታ የሻውወርቅ
ሐራ ዘተዋህዶ በተባለዉ የማህበረ ቅዱሳን መርዝ መርጫ ድረ ገጽ ላይ በምእራብ ሐረርጌ በአሰበ ተፈሪ ቅድስት ልደታ ማርያም ቤተክርስቲያን ቅጽር ግቢ ዉስጥ ከእሁድ ሰንበት ቅዳሴ በኋላ ምእመኑና ማህበረ ካህናቱ የሰበካ ጉባኤ አባላት ምርጫን ለማከናወን በሐገረ ስብከቱ ተይዞ የነበረዉን ፕሮግራም ሰንበት ት/ቤት አባላት ነን ከሚሉ ነገር ግን ሙሉ በሙሉ የማህበረ ቅዱሳን አመራሮችና በጣት በሚቆጠሩ ግለሰቦች የተፈጠረዉን ከኦርቶዶክሳዊ አማኝ ስነምግባር ዉጪ የሆነዉን ሁከት እንደለመደዉ ማህበሩ በአንድ የማህበረ ናታኒም የተሰራ ተንኮል እንደሆነና ከዚሁም ጋር የሐገረ ስብከቱን ስራ አስኪያጅና ጸሀፊ ለመወንጀል የታሰበበት ጽሁፍ አስነበበን፡፡

ያሳዝናል እድሜ ልኩን እንደ ግብር አባቶቹ ጸሐፍት ፈሪሳዊያን/ቤተ አይሁድ/ ለጥፋት የተቋቋመ ማህበር፡፡ መቼ ይሁን እዉነቱን እዉነት ሐሰቱን ሐሰት የሚለዉ፡፡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጸሐፍት ፈሪሳዊያን ተይዞ ሊቀ ካህን ሐና ጋር በቀረበበት ግዜ አንድ ክስተት ተከሰተ ይሄዉም ሊቀ ካህኑ ሐና ኢየሱስ ክርስቶስን ስለ ደቀ መዛሙርቱና ስለ ትምህርቱ ጠየቀዉ፡፡ አምላካዊ መልሱ በግልጥ ለአለም ተናገርኩ አይሁድ ሁሉ በሚሰበሰቡበት  በቤተ መቅደስና በምኩራቦች በግልጽ አስተማርኩኝ በስዉርም ምንም አልተናገርኩም፡፡ ስለምን ትጠይቀኛለህ; የሰሙትን ጠይቅ እነርሱ እኔ የተናገርኩትን ያዉቃሉ አለዉ፡፡ በዚህ ግዜ ግን አንድ አሳዛኝ ክስተት ተከሰተ የሊቀ ካህኑ ሎሌ የነበረ አገልጋይ ኢየሱስ ክርስቶስን ለምን እንዲህ አይነቱን መልስ ለሊቀ ካህኑ ትመልሳለህ ብሎ ጌታን በጥፊ መታዉ፡፡ እጅግ የሚገርመዉ አምላካዊ መልሱ ነዉ፡፡ ኢየሱስም መልሶ #ክፉ ተናግሬ እንደሆንሁ ስለ ክፉ መስክር መልካም ተናግሬ ከሆነ ግን ስለምን ትመታኛለህ አለዉ፡፡$ የዮሀንስ መንጌል ምእራፍ 18፤19-23  ይህንን ጥቅስ የወሰድኩበት አንድ ምክንያት አለኝ፡፡ ማህበረ ቅዱሳን ቤተ ክርስቲያንን እንደ ምሰሶ ደግፎ ይዞ እንደቆመ ራሱን ይቆጥራል' እርሱ እንጂ ሌላ መንፈሳዊ ማህበር ለቤተክርስቲያኒቱ እንደማያስፈልግ ያዉጃል፡፡ 

Thursday, May 9, 2013

አድብቶ ነዳፊው ዳንኤል ክብረት የአውስትራሊያ አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ለመሆን እየሞከረ ነው


(http://awdemihreet.blogspot.com/)ባለሁለት ሚስቱ እና ፈቱ ዳንኤል ክብረት ያፈረሰ ሰው የሚገባውን ማርገጃ አድማቂነት እምቢኝ ብሎ ባልተማረው ትምህርትና በማይመልሰው ተሰጥኦ “ዲያቆን” ተብሎ ለእርሱ ብጤ ጨዋ ማኅበርተኞቹ “ሊቅ” ሆኖ እና “ሊቅ” ተሰኝቶ ከእውነተኛ የቤተክርስቲያን ሊቃውንትና አባቶች ሸሽቶ እንደ እርሱ በሁለት ሀሳብ በገንዘብ እና በዝሙት ከሚያነክሱ አባ አብርሃም እና አባ ኤዎስጣጢዎስን ከመሰሉ ግለሰቦች ተጠግቶ በአድርባይ ብዕሩ እነዚህን የጉድ ሙዳዮች እየሸላለመ የነበረበት ሁኔታ አልበቃ ብሎት አሁን ደግሞ የአውስትራሊያ አህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ለመሆን ደፋ ቀና እያለ ነው፡፡
ማህበርዋን በዋና ጸሐፊነት በመራባቸው ረጅም አመታት ከየዋኃን አባላት ከሚሰበሰበው ገንዘብ እና ከቤተክርስቲያን የድርሻውን ወስዶ በሲኤምሲ ሁለት ቤቶችን የሰራው እና እና ከጊፍት ሪል እስቴት አንድ ቤት በመግዛት የሦስት ቤቶች ባለቤት የሆነው ዳንኤል ክብረት አሁን ደግሞ ሌላ ሦስት ቤት የሚሰራበትን ገንዘብ ከቤተክርስቲያን ለመዝረፍ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ ይህንን ለማሳካት በሲአይኤ ወኪልነት በሚታወቀው እና እንደ እባብ ልስልስ ገላውን እያሳየ የተንኮል ድሩን በሚያደራው እና በቅርቡ የማኅበሩን አንጃ በሀሳብ የተቀላቀለው  በአቶ ባያብል አማላጅነት ጉዳዩ መስመር የያዘለት የመሰለው ዳንኤል ለቅርብ ወዳጆቹ የአውስትራሊያ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ የመሆኑ ጉዳይ ያለቀለት መሆኑን ሲናገር ተሰምቷል፡፡ በዚህም ተቋርጦ የነበረው የዳንኤል እና የባያብል ፍቅር የታደሰ መስሏል፡፡

Thursday, May 2, 2013

‹‹ጎልጎታ››፡- ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር . . .!!!


በፍቅር ለይኩን፡፡

ለዚህ መጣጥፌ የመረጥኩት የእውቁ ሠዓሊና ባለ ቅኔ የገብረ ክርስቶስ ደስታን ‹‹ጎልጎታ››በሚል ርዕስ የተጠበበትን የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የሥነ ስቅለት አስደናቂና ዘመን አይሽሬ (classical) ሥራውን ነው፡፡ የዚህን ገጣሚና ሰዓሊ፣ እጅግ ተወዳጅና ተደናቂው የሆነውን ‹‹የጎልጎታን››ስነ ስቅለት፣ ፍቅርን ተጠበበትን ድንቅ ሥራውን ፅንሰትና ውልደት ታሪክ በአጭሩ ላውጋችኹ፡፡

ገጣሚና ሠዓሊ ገብረ ክርስቶስ ደስታ በኢትዮጵያ ዘመናዊ ሥነ ጥበብ ታሪክ ውስጥ ስሙ ጎልቶ ከሚጠቀሱ የስነ ጥበብ ሰዎች ዘንድ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ እውቅና ታላቅ ሰው ነው፡፡ ገ/ክርስቶስ ዘመናዊ የስዕል ሙያን በአገር ውስጥና በአውሮፓ ከተማረ በኋላ በአገሩ እምብዛም አልቆየም ነበር፡፡ በአገራችን በተከሰተው የ1966 አብዮትናከነደደው የነውጥና የለውጥ እሳት የተነሣ እንደ ብዙዎቹ ኢትዮጵያውያን ምሁራንና ወገኖቹ የእርሱም ዕጣ ፈንታ ስደት ሆኖ ነበር፡፡
ገ/ክርስቶስ በትምህርትና በስደት ሕይወት ለረጅም ዓመታት በባሕረ ማዶ በቆየባቸው ጊዜያት ውስጥ አውሮፓውያኑ ወይም በአጠቃላይ ነጮች ለአፍሪካውያንና ለጥቁር ሕዝቦች ያላቸው ዘረኝነት፣ ንቀትና ጥላቻ በእጅጉ ያብሰለስለውና እረፍት ይነሳው ነበር፡፡

ከምንም በላይ ደግሞ የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ምድር ተምሳሌት፣ በዓለማችን ታሪክ ታይቶና፣ ተሰምቶ በማይታወቅ ጀግንነትና ወኔ ኢትዮጵያውያን፣ አባቶቹ ወራሪውን የኢጣሊያንን ቅኝ ገዢ ኃይል በዓድዋ ጦር ግንባር በአኩሪ ጀግንነት አሳፍረው የመለሱ ኃያላን መሆናቸውን አሳምሮ ለሚያውቀው ገ/ክርስቶስ ይህ የአውሮፓውኑ ትምክህትና ንቀት ከመገረምም በላይ ሆኖበት ነበር፡፡

Monday, April 29, 2013

አባ አብርሃም እና ማኅበረ ቅዱሳን በአሜሪካ ያለውን የሀገረ ስብከት ጽ/ቤት እንዲያስረክቡ ቋሚ ሲኖዶሱ ወሰነ



(http://awdemihreet.blogspot.com/) በማኅበረ ቅዱሳን አይዞህ ባይነት የአሜሪካውን ሃገረ ስብከት ጽ/ቤት ለብጹዕ አቡነ ፋኑኤል አላስረክብም ብለው የነበሩት አባ አብርሃም የሀገረ ስብከቱን ጽ/ቤት እንዲያስረክቡ ቋሚ ሲኖዶሱ ወሰነ፡፡ ይህ በቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ፊርማ የወጣው እና አድራሻውን ለአባ አብርሃም ያደረገው ደብዳቤ እንዳስታወቀው አባ አብርሃም ሀገረ ስብከቱን በዝውውር ለቀው ከወጡ በኃላ የሀገረ ስብከቱን ጽ/ቤት አላስረክብም ማለታቸው ህገ ወጥ ድርጊት ነው፡፡


አባ አብርሃም ቤተክርሰቲያን አንዲት መሆንዋን መረዳት ከብዷቸው እና እሳቸውን ለማዘዝ ሙሉ ስልጣን ያለውን ቅዱስ ሲኖዶስ ተጋፍተው ላለፉት ሁለት አመታት የሀገረ ስብከቱን ጽ/ቤት አላስረክብም በማለት በሀገረ ስብከቱ ውስጥ የሽፍታ ሠራዊት ማስፈራቸው አስገራሚ ሆኖ ሰንብቷል፡፡ እኚህ ጉድ አያል     ቅበት የሆኑት ጳጳስ መንፈሳዊ አገልግሎት የሚሳካው እሺ ብሎ በመታዘዝ መሆኑ ከዲቁና እስከ ጵጵስና ድረስ አለመረዳታቸው በብዙዎች ዘንድ የሚያስተዛዝብ ሆኗል፡፡ 

Thursday, April 25, 2013

የቤተ ክህነቱ የሰሞኑ ሁኔታ እና የማኅበረ ቅዱሳን ጫጫታ



 http://awdemihreet.blogspot.com/
ከጥቅምቱ ሲኖዶስ ስብሰባ ወዲህ በአሉበት ሁኔታ መቆየት አለመቆየታቸው እያሰጋቸው የመጣው አቶ ተስፋዬ ውብሸት እና አቶ እስክንድር ገብረክርስቶስ ከሥራ ከመሰናበታቸው በፊት ጠቀም ያለ ገንዘብ ለማግኘት እያደረጉ ያለው እንቅስቃሴ ሁሉ እየከሸፈባቻ ሲቸገሩ ያላቸውን ቀሪ የገንዘብ ምንጭ ማኅበረ ቅዱሳንን የሚያስደስት እቅድ ይነድፋሉ፡፡ እሱም ለቅዱስ ፓትርያርኩ የውጭ ግንኙነት ኃላፊን ከማኅበረ ቅዱሳን ሰዎች መካከል መንግስት ሾመልዎ በማለት ማስቀመጥ ነው፡፡
ይህንን እቅዳቸውን ከማኅበሩ አመራር ጋር ከተነጋገሩበት በኋላ በአዲስ አበባ መስተዳድር የሚሰራውን አቶ ታምሩ አበራ የተባለውን ግለሰብ ያጫሉ፡፡ ይህን ግለሰብ ለፓትርያርኩ መንግስት መደበልዎ ብሎ ማቅረብ እና ከዚያም በመንግስት ስም ተከልሎ የማኅበረ ቅዱሳንን ፍላጎት በመንግስት ስም ለማስፈጸም  አስፈላጊውን ሁሉ አድርገው ለቅዱስ ፓትርያርኩ ያቀርባሉ፡፡ ይህ አካሄድ እውነት እንዳልሆነ የተረዱት የቤተክርስቲያን ልጆችም ሁኔታውን በትኩረት በመከታተል ሀሳቡን የሚያከሽፍ እንቅስቃሴ ይጀምራሉ፡፡ እንቅስቃሴው ውጤት አግኝቶም መንግስት የመደበውም ሆነ የሚመድበው ሰው እንደሌለ ለቅዱስ ፓትርያርኩ በአቶ አባይ ጸሀዬ በኩል ያስታውቃል፡፡ 

በዚህ የተናደዱት እነ ተስፋዬ እና እስክንድር ከማኅበረ ቅዱሳን አንጃ ብሎግ ከሆነችው ሐራ ተዋህዶ ጋር በመቀናጀት የስም ማጥፋት ሥራውን ጀመሩ፡፡
ሀራ ተዋህዶ ሲቆጫት ሲያንገበግባት፣ የሚያደርጋትን ሲያሳጣትና ማኅበረ ቅዱሳን የፈለገው ነገር አልሳካ ሲላት ያረረውንም የመረረውንም፣ ያልተባለውንም ነገር ሁሉ “ሰበር” ደንገር እያለች እንደ ታላላቅ ወንድሞችዋ እነ ደጀ ሰላም መዘባረቅ ጀምራለች፡፡

ለአንባቢዎቻችን



ብሎጋችን ለተወሰነ ጊዜ ዝምታን መርጣ ቆይታ ነበር፡፡ በዝምታው  ወቅት በርካታ አንባቢዎች በኢሜልና በአስተያየት ለሰጣችሁን ምክርና ማበረታቻ እያመሰገንን አሁን ግን እንደገና በቤተክህነት አካባቢ ያሉ ዘገባዎችን የምንቀጥል መሆኑን እንገልጣለን፡፡

Thursday, February 21, 2013

ኢሳት ይጠየቅልኝ!

ዝርዝር ጥልቀት ያለው ሐተታ ቀርቶ የውጣ ቃልም ብትሆን ስለ ኢሳት አንጻራዊ አመለካከት ማንጸባረቅ፡ ተቋሙ እየተከተለው ያለውን አሰራርና እየሄደበት ያለው ማንንም የማይጠቅም መንገድ እንደ ዜጋ በግልጽ መናገር: ትንፍሽ ማለት በተለይ "ይውደም!" ከተባለ "ይውደም!"- "ይቅደም!" ከተባለም እንዲሁ በተመሳሳይ ድምጽ "እንዴትና? ለምን?" በሌለበት ሁኔታ "ይውደም!" በማለት ድምጹን በማስተጋባት በሚታወቀው ማህበረሰብ አካባቢ ዘንዳ ምን ዓይነት ስም ሊያሰጥ እንደሚችል በሚገባ ጠንቅቄ አውቃለሁ። የደርግ ወታደራዊ መንግስት ቀን ጨለማ ሳይል የንጹሐን ዜጎች ደም ደመ ከልብ ሲያደርግና በገዛ ሕዝቡ በአደባባይ በጥይት ሲደበድብ/ሲረሽን አገኘሁበት የሚለው ክስ አንዱ "ጸረ አብዮት ነው!በማለት ነበር ሲሉ ከሞት ያመለጡ ምስክሮች እንደሚናገሩት ማለት ነው። ያም ሆነ ይህ መስመሩ ስለ ለቀቀና አቅጣጫው ክፉኛ ስቶ ስለሚገኘው: ታማኝነት የጎደለበት፡ ከምንም በላይ ደግሞ የሞያው ስነ ምግባር በሚጣረስ መልኩ ሆነ ተብሎ እየተደረገ ያለው የኢሳት አሰራር ጭብጥ ላይ የተመረኮዘ ተጨባጭ ሃሳብ ይዤ መመጎቴ ተከትሎ በጸሐፊው /ለሚለጠፉ ታቤላዎች አግባብነት የለውም ችግሩም ይቀርፈዋል የሚል እምነት የለኝም።
የኢ////ያን በተመልከተ በተለይ ከወቅቱ ጋር በተያያዘ የሃይማኖት መሪዎች የእርስ በርስ የመተረማመሱ ነገር እንዲሁም
በሁለቱም የሃይማኖት መሪዎች በኩል ከመንፈሳዊነት ይልቅ እልከኝነት የተሞለበት ስብእናቸው አይሎ ከመውጣቱ የተነሳ የከሸፈውን እርቀ ሰላም በኢሳት በኩል ያለ አንዳች ተጨባጭና ደረቅ ማስረጃ የኢትዮጵያ መንግስት ተጠያቂ ለማድረግ የተሰሩ "ዜናዎችና ሐተታዎች" ብዛቱ ስፍር ቁጥር የለውም። ይህ የምለው ደግሞ እንደ ወንጌል አገልጋይነቴ እውነቱ እውነት ለማለት እንጅ ለመንግስት ጥብቅና ለመቆም ቃጥቶችም አይደለም። ቀደም ሲል በእኔ በኩልም ሆነ በሌሎች የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆችና መምህራን አማካኝነት ከዚህ ሁሉ የሃይማኖት መሪዎች ትርምስ ጀርባ ለመልካም ነገር የሚያበቃ አቅም ባይኖረውም ለሁከትና ለረብሻ ግን የሚስተካከለው የሌለው "ማህበረ ቅዱሳን" በማለት ራሱን የሚጠራ ስመ መንፈሳዊ አጽራረ ጽድቅ ድርጅት የኢ////ያን የማፈራረስ ዓላማ አንዱ ስትራቴጂ መሆኑ በተጨባጭ ሲነገር መክረሙን የምንዘናጋው እውነት አይደለም።