Monday, August 5, 2013

በእጅ አዙር የቤተክርስቲያኒቱን መዋቅር መቆጣጠር የሚፈልገዉ የጸሐፍት ፈሪሳዊያን ጥርቅሙ ማህበረ ቅዱሳን በአሰበ ተፈሪ ድብቅ ሴራዉ ተጋለጠ

Read In PDF: Asebeteferi
 ከመሪጌታ የሻውወርቅ
ሐራ ዘተዋህዶ በተባለዉ የማህበረ ቅዱሳን መርዝ መርጫ ድረ ገጽ ላይ በምእራብ ሐረርጌ በአሰበ ተፈሪ ቅድስት ልደታ ማርያም ቤተክርስቲያን ቅጽር ግቢ ዉስጥ ከእሁድ ሰንበት ቅዳሴ በኋላ ምእመኑና ማህበረ ካህናቱ የሰበካ ጉባኤ አባላት ምርጫን ለማከናወን በሐገረ ስብከቱ ተይዞ የነበረዉን ፕሮግራም ሰንበት ት/ቤት አባላት ነን ከሚሉ ነገር ግን ሙሉ በሙሉ የማህበረ ቅዱሳን አመራሮችና በጣት በሚቆጠሩ ግለሰቦች የተፈጠረዉን ከኦርቶዶክሳዊ አማኝ ስነምግባር ዉጪ የሆነዉን ሁከት እንደለመደዉ ማህበሩ በአንድ የማህበረ ናታኒም የተሰራ ተንኮል እንደሆነና ከዚሁም ጋር የሐገረ ስብከቱን ስራ አስኪያጅና ጸሀፊ ለመወንጀል የታሰበበት ጽሁፍ አስነበበን፡፡

ያሳዝናል እድሜ ልኩን እንደ ግብር አባቶቹ ጸሐፍት ፈሪሳዊያን/ቤተ አይሁድ/ ለጥፋት የተቋቋመ ማህበር፡፡ መቼ ይሁን እዉነቱን እዉነት ሐሰቱን ሐሰት የሚለዉ፡፡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጸሐፍት ፈሪሳዊያን ተይዞ ሊቀ ካህን ሐና ጋር በቀረበበት ግዜ አንድ ክስተት ተከሰተ ይሄዉም ሊቀ ካህኑ ሐና ኢየሱስ ክርስቶስን ስለ ደቀ መዛሙርቱና ስለ ትምህርቱ ጠየቀዉ፡፡ አምላካዊ መልሱ በግልጥ ለአለም ተናገርኩ አይሁድ ሁሉ በሚሰበሰቡበት  በቤተ መቅደስና በምኩራቦች በግልጽ አስተማርኩኝ በስዉርም ምንም አልተናገርኩም፡፡ ስለምን ትጠይቀኛለህ; የሰሙትን ጠይቅ እነርሱ እኔ የተናገርኩትን ያዉቃሉ አለዉ፡፡ በዚህ ግዜ ግን አንድ አሳዛኝ ክስተት ተከሰተ የሊቀ ካህኑ ሎሌ የነበረ አገልጋይ ኢየሱስ ክርስቶስን ለምን እንዲህ አይነቱን መልስ ለሊቀ ካህኑ ትመልሳለህ ብሎ ጌታን በጥፊ መታዉ፡፡ እጅግ የሚገርመዉ አምላካዊ መልሱ ነዉ፡፡ ኢየሱስም መልሶ #ክፉ ተናግሬ እንደሆንሁ ስለ ክፉ መስክር መልካም ተናግሬ ከሆነ ግን ስለምን ትመታኛለህ አለዉ፡፡$ የዮሀንስ መንጌል ምእራፍ 18፤19-23  ይህንን ጥቅስ የወሰድኩበት አንድ ምክንያት አለኝ፡፡ ማህበረ ቅዱሳን ቤተ ክርስቲያንን እንደ ምሰሶ ደግፎ ይዞ እንደቆመ ራሱን ይቆጥራል' እርሱ እንጂ ሌላ መንፈሳዊ ማህበር ለቤተክርስቲያኒቱ እንደማያስፈልግ ያዉጃል፡፡ 

Thursday, May 9, 2013

አድብቶ ነዳፊው ዳንኤል ክብረት የአውስትራሊያ አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ለመሆን እየሞከረ ነው


(http://awdemihreet.blogspot.com/)ባለሁለት ሚስቱ እና ፈቱ ዳንኤል ክብረት ያፈረሰ ሰው የሚገባውን ማርገጃ አድማቂነት እምቢኝ ብሎ ባልተማረው ትምህርትና በማይመልሰው ተሰጥኦ “ዲያቆን” ተብሎ ለእርሱ ብጤ ጨዋ ማኅበርተኞቹ “ሊቅ” ሆኖ እና “ሊቅ” ተሰኝቶ ከእውነተኛ የቤተክርስቲያን ሊቃውንትና አባቶች ሸሽቶ እንደ እርሱ በሁለት ሀሳብ በገንዘብ እና በዝሙት ከሚያነክሱ አባ አብርሃም እና አባ ኤዎስጣጢዎስን ከመሰሉ ግለሰቦች ተጠግቶ በአድርባይ ብዕሩ እነዚህን የጉድ ሙዳዮች እየሸላለመ የነበረበት ሁኔታ አልበቃ ብሎት አሁን ደግሞ የአውስትራሊያ አህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ለመሆን ደፋ ቀና እያለ ነው፡፡
ማህበርዋን በዋና ጸሐፊነት በመራባቸው ረጅም አመታት ከየዋኃን አባላት ከሚሰበሰበው ገንዘብ እና ከቤተክርስቲያን የድርሻውን ወስዶ በሲኤምሲ ሁለት ቤቶችን የሰራው እና እና ከጊፍት ሪል እስቴት አንድ ቤት በመግዛት የሦስት ቤቶች ባለቤት የሆነው ዳንኤል ክብረት አሁን ደግሞ ሌላ ሦስት ቤት የሚሰራበትን ገንዘብ ከቤተክርስቲያን ለመዝረፍ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ ይህንን ለማሳካት በሲአይኤ ወኪልነት በሚታወቀው እና እንደ እባብ ልስልስ ገላውን እያሳየ የተንኮል ድሩን በሚያደራው እና በቅርቡ የማኅበሩን አንጃ በሀሳብ የተቀላቀለው  በአቶ ባያብል አማላጅነት ጉዳዩ መስመር የያዘለት የመሰለው ዳንኤል ለቅርብ ወዳጆቹ የአውስትራሊያ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ የመሆኑ ጉዳይ ያለቀለት መሆኑን ሲናገር ተሰምቷል፡፡ በዚህም ተቋርጦ የነበረው የዳንኤል እና የባያብል ፍቅር የታደሰ መስሏል፡፡

Thursday, May 2, 2013

‹‹ጎልጎታ››፡- ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር . . .!!!


በፍቅር ለይኩን፡፡

ለዚህ መጣጥፌ የመረጥኩት የእውቁ ሠዓሊና ባለ ቅኔ የገብረ ክርስቶስ ደስታን ‹‹ጎልጎታ››በሚል ርዕስ የተጠበበትን የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የሥነ ስቅለት አስደናቂና ዘመን አይሽሬ (classical) ሥራውን ነው፡፡ የዚህን ገጣሚና ሰዓሊ፣ እጅግ ተወዳጅና ተደናቂው የሆነውን ‹‹የጎልጎታን››ስነ ስቅለት፣ ፍቅርን ተጠበበትን ድንቅ ሥራውን ፅንሰትና ውልደት ታሪክ በአጭሩ ላውጋችኹ፡፡

ገጣሚና ሠዓሊ ገብረ ክርስቶስ ደስታ በኢትዮጵያ ዘመናዊ ሥነ ጥበብ ታሪክ ውስጥ ስሙ ጎልቶ ከሚጠቀሱ የስነ ጥበብ ሰዎች ዘንድ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ እውቅና ታላቅ ሰው ነው፡፡ ገ/ክርስቶስ ዘመናዊ የስዕል ሙያን በአገር ውስጥና በአውሮፓ ከተማረ በኋላ በአገሩ እምብዛም አልቆየም ነበር፡፡ በአገራችን በተከሰተው የ1966 አብዮትናከነደደው የነውጥና የለውጥ እሳት የተነሣ እንደ ብዙዎቹ ኢትዮጵያውያን ምሁራንና ወገኖቹ የእርሱም ዕጣ ፈንታ ስደት ሆኖ ነበር፡፡
ገ/ክርስቶስ በትምህርትና በስደት ሕይወት ለረጅም ዓመታት በባሕረ ማዶ በቆየባቸው ጊዜያት ውስጥ አውሮፓውያኑ ወይም በአጠቃላይ ነጮች ለአፍሪካውያንና ለጥቁር ሕዝቦች ያላቸው ዘረኝነት፣ ንቀትና ጥላቻ በእጅጉ ያብሰለስለውና እረፍት ይነሳው ነበር፡፡

ከምንም በላይ ደግሞ የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ምድር ተምሳሌት፣ በዓለማችን ታሪክ ታይቶና፣ ተሰምቶ በማይታወቅ ጀግንነትና ወኔ ኢትዮጵያውያን፣ አባቶቹ ወራሪውን የኢጣሊያንን ቅኝ ገዢ ኃይል በዓድዋ ጦር ግንባር በአኩሪ ጀግንነት አሳፍረው የመለሱ ኃያላን መሆናቸውን አሳምሮ ለሚያውቀው ገ/ክርስቶስ ይህ የአውሮፓውኑ ትምክህትና ንቀት ከመገረምም በላይ ሆኖበት ነበር፡፡

Monday, April 29, 2013

አባ አብርሃም እና ማኅበረ ቅዱሳን በአሜሪካ ያለውን የሀገረ ስብከት ጽ/ቤት እንዲያስረክቡ ቋሚ ሲኖዶሱ ወሰነ



(http://awdemihreet.blogspot.com/) በማኅበረ ቅዱሳን አይዞህ ባይነት የአሜሪካውን ሃገረ ስብከት ጽ/ቤት ለብጹዕ አቡነ ፋኑኤል አላስረክብም ብለው የነበሩት አባ አብርሃም የሀገረ ስብከቱን ጽ/ቤት እንዲያስረክቡ ቋሚ ሲኖዶሱ ወሰነ፡፡ ይህ በቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ፊርማ የወጣው እና አድራሻውን ለአባ አብርሃም ያደረገው ደብዳቤ እንዳስታወቀው አባ አብርሃም ሀገረ ስብከቱን በዝውውር ለቀው ከወጡ በኃላ የሀገረ ስብከቱን ጽ/ቤት አላስረክብም ማለታቸው ህገ ወጥ ድርጊት ነው፡፡


አባ አብርሃም ቤተክርሰቲያን አንዲት መሆንዋን መረዳት ከብዷቸው እና እሳቸውን ለማዘዝ ሙሉ ስልጣን ያለውን ቅዱስ ሲኖዶስ ተጋፍተው ላለፉት ሁለት አመታት የሀገረ ስብከቱን ጽ/ቤት አላስረክብም በማለት በሀገረ ስብከቱ ውስጥ የሽፍታ ሠራዊት ማስፈራቸው አስገራሚ ሆኖ ሰንብቷል፡፡ እኚህ ጉድ አያል     ቅበት የሆኑት ጳጳስ መንፈሳዊ አገልግሎት የሚሳካው እሺ ብሎ በመታዘዝ መሆኑ ከዲቁና እስከ ጵጵስና ድረስ አለመረዳታቸው በብዙዎች ዘንድ የሚያስተዛዝብ ሆኗል፡፡ 

Thursday, April 25, 2013

የቤተ ክህነቱ የሰሞኑ ሁኔታ እና የማኅበረ ቅዱሳን ጫጫታ



 http://awdemihreet.blogspot.com/
ከጥቅምቱ ሲኖዶስ ስብሰባ ወዲህ በአሉበት ሁኔታ መቆየት አለመቆየታቸው እያሰጋቸው የመጣው አቶ ተስፋዬ ውብሸት እና አቶ እስክንድር ገብረክርስቶስ ከሥራ ከመሰናበታቸው በፊት ጠቀም ያለ ገንዘብ ለማግኘት እያደረጉ ያለው እንቅስቃሴ ሁሉ እየከሸፈባቻ ሲቸገሩ ያላቸውን ቀሪ የገንዘብ ምንጭ ማኅበረ ቅዱሳንን የሚያስደስት እቅድ ይነድፋሉ፡፡ እሱም ለቅዱስ ፓትርያርኩ የውጭ ግንኙነት ኃላፊን ከማኅበረ ቅዱሳን ሰዎች መካከል መንግስት ሾመልዎ በማለት ማስቀመጥ ነው፡፡
ይህንን እቅዳቸውን ከማኅበሩ አመራር ጋር ከተነጋገሩበት በኋላ በአዲስ አበባ መስተዳድር የሚሰራውን አቶ ታምሩ አበራ የተባለውን ግለሰብ ያጫሉ፡፡ ይህን ግለሰብ ለፓትርያርኩ መንግስት መደበልዎ ብሎ ማቅረብ እና ከዚያም በመንግስት ስም ተከልሎ የማኅበረ ቅዱሳንን ፍላጎት በመንግስት ስም ለማስፈጸም  አስፈላጊውን ሁሉ አድርገው ለቅዱስ ፓትርያርኩ ያቀርባሉ፡፡ ይህ አካሄድ እውነት እንዳልሆነ የተረዱት የቤተክርስቲያን ልጆችም ሁኔታውን በትኩረት በመከታተል ሀሳቡን የሚያከሽፍ እንቅስቃሴ ይጀምራሉ፡፡ እንቅስቃሴው ውጤት አግኝቶም መንግስት የመደበውም ሆነ የሚመድበው ሰው እንደሌለ ለቅዱስ ፓትርያርኩ በአቶ አባይ ጸሀዬ በኩል ያስታውቃል፡፡ 

በዚህ የተናደዱት እነ ተስፋዬ እና እስክንድር ከማኅበረ ቅዱሳን አንጃ ብሎግ ከሆነችው ሐራ ተዋህዶ ጋር በመቀናጀት የስም ማጥፋት ሥራውን ጀመሩ፡፡
ሀራ ተዋህዶ ሲቆጫት ሲያንገበግባት፣ የሚያደርጋትን ሲያሳጣትና ማኅበረ ቅዱሳን የፈለገው ነገር አልሳካ ሲላት ያረረውንም የመረረውንም፣ ያልተባለውንም ነገር ሁሉ “ሰበር” ደንገር እያለች እንደ ታላላቅ ወንድሞችዋ እነ ደጀ ሰላም መዘባረቅ ጀምራለች፡፡

ለአንባቢዎቻችን



ብሎጋችን ለተወሰነ ጊዜ ዝምታን መርጣ ቆይታ ነበር፡፡ በዝምታው  ወቅት በርካታ አንባቢዎች በኢሜልና በአስተያየት ለሰጣችሁን ምክርና ማበረታቻ እያመሰገንን አሁን ግን እንደገና በቤተክህነት አካባቢ ያሉ ዘገባዎችን የምንቀጥል መሆኑን እንገልጣለን፡፡

Thursday, February 21, 2013

ኢሳት ይጠየቅልኝ!

ዝርዝር ጥልቀት ያለው ሐተታ ቀርቶ የውጣ ቃልም ብትሆን ስለ ኢሳት አንጻራዊ አመለካከት ማንጸባረቅ፡ ተቋሙ እየተከተለው ያለውን አሰራርና እየሄደበት ያለው ማንንም የማይጠቅም መንገድ እንደ ዜጋ በግልጽ መናገር: ትንፍሽ ማለት በተለይ "ይውደም!" ከተባለ "ይውደም!"- "ይቅደም!" ከተባለም እንዲሁ በተመሳሳይ ድምጽ "እንዴትና? ለምን?" በሌለበት ሁኔታ "ይውደም!" በማለት ድምጹን በማስተጋባት በሚታወቀው ማህበረሰብ አካባቢ ዘንዳ ምን ዓይነት ስም ሊያሰጥ እንደሚችል በሚገባ ጠንቅቄ አውቃለሁ። የደርግ ወታደራዊ መንግስት ቀን ጨለማ ሳይል የንጹሐን ዜጎች ደም ደመ ከልብ ሲያደርግና በገዛ ሕዝቡ በአደባባይ በጥይት ሲደበድብ/ሲረሽን አገኘሁበት የሚለው ክስ አንዱ "ጸረ አብዮት ነው!በማለት ነበር ሲሉ ከሞት ያመለጡ ምስክሮች እንደሚናገሩት ማለት ነው። ያም ሆነ ይህ መስመሩ ስለ ለቀቀና አቅጣጫው ክፉኛ ስቶ ስለሚገኘው: ታማኝነት የጎደለበት፡ ከምንም በላይ ደግሞ የሞያው ስነ ምግባር በሚጣረስ መልኩ ሆነ ተብሎ እየተደረገ ያለው የኢሳት አሰራር ጭብጥ ላይ የተመረኮዘ ተጨባጭ ሃሳብ ይዤ መመጎቴ ተከትሎ በጸሐፊው /ለሚለጠፉ ታቤላዎች አግባብነት የለውም ችግሩም ይቀርፈዋል የሚል እምነት የለኝም።
የኢ////ያን በተመልከተ በተለይ ከወቅቱ ጋር በተያያዘ የሃይማኖት መሪዎች የእርስ በርስ የመተረማመሱ ነገር እንዲሁም
በሁለቱም የሃይማኖት መሪዎች በኩል ከመንፈሳዊነት ይልቅ እልከኝነት የተሞለበት ስብእናቸው አይሎ ከመውጣቱ የተነሳ የከሸፈውን እርቀ ሰላም በኢሳት በኩል ያለ አንዳች ተጨባጭና ደረቅ ማስረጃ የኢትዮጵያ መንግስት ተጠያቂ ለማድረግ የተሰሩ "ዜናዎችና ሐተታዎች" ብዛቱ ስፍር ቁጥር የለውም። ይህ የምለው ደግሞ እንደ ወንጌል አገልጋይነቴ እውነቱ እውነት ለማለት እንጅ ለመንግስት ጥብቅና ለመቆም ቃጥቶችም አይደለም። ቀደም ሲል በእኔ በኩልም ሆነ በሌሎች የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆችና መምህራን አማካኝነት ከዚህ ሁሉ የሃይማኖት መሪዎች ትርምስ ጀርባ ለመልካም ነገር የሚያበቃ አቅም ባይኖረውም ለሁከትና ለረብሻ ግን የሚስተካከለው የሌለው "ማህበረ ቅዱሳን" በማለት ራሱን የሚጠራ ስመ መንፈሳዊ አጽራረ ጽድቅ ድርጅት የኢ////ያን የማፈራረስ ዓላማ አንዱ ስትራቴጂ መሆኑ በተጨባጭ ሲነገር መክረሙን የምንዘናጋው እውነት አይደለም።