Ayne merfe
በዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል
እስራኤል በርካታ እግዚአብሔር የሚያስከፉ ከጠየቃቸው ጥያቄዎች መካከል ሳሙኤል በሸመገለ ጊዜ ንጉሥ ስጠን በማለት ያቀረቡት
ጥያቄ ተጠቃሽ ነው። ይህን የእስራኤል አሳብና ጥያቄም እግዚአብሔር ክፉኛ እንዳሳዘነና ለጥያቄአቸውም በእስራኤል ሁሉ ላይ ንጉሥ
ይሆን ዘንድ አህያ ፍለጋ የወጣውን የቢንያማዊው የቂስ ልጅ ሳዖል ንጉሥ አድርጎ እንደሰጣቸው በቅድሳት መጻህፍት በስፋት ታትቶ እናገኘዋለን።
ንጉሥ ሳኦል በዋናነት የሚታወቀው ምንም እንኳን በእግዚአብሔር ፈቃድ የተሾመ ንጉሥ ቢሆንም እግዚአብሔር በመታዘዝ ባለመጽናቱ እግዚአብሔር
የናቀው ከዚህ ጊዜ ጀምሮም ክፉ መንፈስ ያደረበትና መናፍስት ጥሪ ወደ ሆነች ሴት የሄደም ፍጻሜው ያላማረለት ታሪኩ ባነበብት ቁጥር
ልብ የሚሰብር ንጉሥ ነው።
በእርግጥ የሲኖዶስ አመሰራረትና አነሳስ በተመለከተ በመጠኑም ቢሆን ከሐዋሪያት ሥራ መጽሐፍ ለመረዳት እንደሚቻለው ዓላማውና
ግቡ የእግዚአብሔር ክብር ለመግለጥና እውነት የሆነችውን የጽድቅ መንግሥቱም በምድር ሁሉ ላይ ለማስፋት እንደሆነ/እንደነበር ለመረዳት አያዳግትም። በሌላ መልኩ ያየነው
እንደሆነም የአባቶች መሰባሰብና በህብረት መቀመጥ ጥቅሙ የሚያጠያይቅ አይሆንም።
ወደ ነባራዊው የራሳችን ጉዳይ የተመለስን እንደሆነ በአንፃሩ ነገሩ የተገላቢጦሽ ሆኖ ነው የምናገኘው። ሁላችን እንደምናውቀው
ሲኖዶስ ተሰበሰበ በተባለ ቁጥር ለመስማት የምንጓጓው ዛሬስ በተራው ማን ይወገር ይሆን?፣ ማን ማንን ይዘልፍና ይዘነጥል ይሆን?
የሚል ነው። እውነትም ስብሰባው በተጠናቀቀበት ቅጽበት ከወደ መገናኛ ብዙሐን በኩል የምንሰማውም "ለ … ያህል ቀናት
ስብሰባውን ሲያካሂድ የሰነበተው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት ስብሰባውን አጠናቀቀ። ስብሰባው በርካታ ትእይንቶች
የታየበት ሲሆን አቡነ እገሌ አቡነ እገሌ … ሲሉ መዝለፋቸውን፣ …
የውስጥ አዋቂ ምንጮችቻችን በደረሱን ዘጋባ ለማወቅ ተችለዋል" ጨምሮ ሌሎች በርካታ የማይሰማ አሳዛኝ ነገር የለም።
