Friday, May 18, 2012

በማኅበረ ቅዱሳን ተጽዕኖ ህልውናውን የካደ ኮሌጅ

Click here to read in PDF   
PDF: court decision
  • አንድ የቤተክርስቲያንን ልጅ ለማባረር ሲል እራሱን ሕጋዊ ሰውነት የሌለው አድርጎ የሚያሳይ የክስ ወረቀት ለሰበር ሰሚ ችሎት አቀረበ
  • ኮሌጁበሰበር ሰሚ ችሎት ከረታ ለተማሪዎቹ ከፍተኛ አደጋ አለው
የኢዮቤልዩ በዓሉን ለማክበር ጥቂት ዓመታት የቀሩትና ከተመሰረተ 69 ዓመት የሆነው የቅድስት ስላሴ ኮሌጅ ከመምህር አሰግድ ሣህሉ ጋር ባለው የሕግ ክርክር በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትና በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የገጠመውን ሽንፈት ሽሮ በድል እንድወጣ ያስችለኛል ያለውን የይግባኝ አቤቱታ ለሰበር ሰሚ ሲያቀርብ ሕጋዊ ሰውነት የሌለኝና ከአንድ ግለሰብ እንኳ ያነስኩ ነኝ ሲል ህልውናውን ካደ።
የኮሌጁ ጠበቃ እያለች የሕግ ክርክሩን በራሴ በኩል ልምራው የሚለው ማኅበረ ቅዱሳን አመራር በሆነው ደስታ በርሔ በተባለ ጠበቃ በኩል የሕግ ክርክሩን ቢቀጥልም በስር ፍርድ ቤት የገጠመውን ሽንፈት ይሽርልኛል ብሎ ላለፉት አምስት ወራት ሲያስብ ቆይቶ ባቀረበው አቤቱታ በተራ ቁጥር 2 ላይ ያለው የአቤቱታው ዝርዝር በሚለው አንቀጽ በግልጽ ህጋዊ ሰውነት የሌለው ኮሌጅ ነው ሲል የኮሌጁን ህልውና ክዷል።
እኔ ያልኩት ብቻ ትክክል ነው የጠላሁትም መናፍቅ ነው የሚል መመሪያ ያለው ማቅ ፍላጎቱ እንዲሳካ የማያደርገው ነገር እንደሌለው የሚያስረዳው አቤቱታ የ69 አመቱን አንጋፋ ኮሌጅ እዚህ ግባ የሚባል ካሪኩለም የሌለው እናደረጃውም የትምህርት ሚኒስቴርን ተቀባይነት የማይመጥን በማለት የኮሌጁ ተማሪ የሆነው መምህር አሰግድ ይባረርልኝ የሚለው አቤቱታ ይህን ይመስላል።
የአቤቱታው ዝርዝር
በመሠረቱ አመልካች ኮሌጅ በራሱ ሕጋዊ ሰውነት የለውም፡፡ እንደ ሌሎች የትምህርት ተቋማት በትምህርት ሚኒስቴር ተመዝግቦና የንግድ ፈቃድ አውጥቶ የሚያስተምር ተቋም አይደለም፡፡ ቀደም ሲል በነበረው መንግስት ተዘግቶ ከቆየ በኋላ በቀጥታ በመንግስት ፈቃድ ቤተክርስቲያኗ ከፍታ የሐይማኖቷን ተከታዮች ለማነጽ መምህራንን የምታፈራበት ነው፡፡ የሚሰጠው የትምህርት ዓይነትም ሆነ ብዛት በትምህርት ሚኒስቴር ቁጥጥር የሚደረግበት አይደለም፡፡ በመሆኑም በስሙ ሊከሰሰም ሆነ ሊፈረድበት አይችልም፡፡ በሕግ ‹‹ሰው›› የሚለውን መስፈረትም አያሟላምና፡፡ ስለዚህ የስር ፍ/ቤቶች ጉዳዩን ተቀብለው ማስተናገድም ሆነ አስገዳጅ ውሳኔ መስጠታቸው መሠረታዊ የህግ ስህተት ነው፡፡
ይህ አቤቱታ ቀላል የማይባሉ ስህተቶች ያሉትና እራሱ ኮሌጁ ባለፉት አመታት ባስተማርኩዋቸው ተማሪዎቼ ደረስኩበት የሚለውን ስኬት የሚንድና ተማሪዎቹ ወደ ሌላ የትምህርት ተቋማት ሄደው ለመማር ያላቸውን ፍላጎት ከንቱ የሚያደርግ ነው። አንድ የቤተክርስቲያን ልጅን ካላባረርኩ በሚል ህልውና እስከመካድ ድረስ የደረሰ አቤቱታ ማቅረብ እጅግ በጣም አሳፋሪ የሆነ ተግባር ነው።

የቅዱስ ሲኖዶስ ሰባተኛ ቀን ውሎ

Click here to read in PDF
  • አንዳንዶቹን ግረለሰቦች ሊቃውነት  ጉባኤ ጠርቶ ስላላነጋገራቸው ጠርቶ እንዲያነጋግር ታዘዘ
  • አቡነ ገብርኤል ከአዋሳ አይነሱም
  • የሰንበት ማደራጀውና የማኅበረ ቅዱሳን ጉዳይ ታየ
  • ዲ/ን አሸነፊ መኮንን በፍጹም ይወገዝ ተብሎ አልቀረበም
በትናንትናው ዕለት በተደረገው የሲኖዶስ ስብሰባ ከተነጋገራባቸው ጉዳዮች አንዱ ማኅበረ ቅዱሳን እንዲወገዙ ከቋመጠባቸው ግለሰቦች አንዳቸውም ሳይወገዙ እንደ ገና መታየት ያለባቸው ነገሮች እንዲታዩና ሲኖዶሱ ሊቃውነት ጉባኤው ሰዎቹን ጠርቶ በጥንቃቄ መርምሮ ይወሰወን የሚለውን ባለሟላቱ እንደገና ያላነጋገሩዋቸውን ሰዎች እንዲያነጋግሩ ታዘዘ። 

የአባ ሰረቀ እና የዲ/ን በጋሻው የውግዘት ሀሳብ እንደአልቀረበባቸውታውቋል። በጋሻው በትናንትናው ዕለት ሊቃውንት ጉባኤ ሊያነጋግረው ፈልጎ ተጠርቶ የነበረ ቢሆንም ሊቃውንት ጉባኤው ራሱ በሲኖዶሱ በመጠራቱ ሳያነጋግሩት ቀርተዋል። ደጀ ሰላም ዲ/ን በጋሻው ሊለማመጥ ሄደ ያለው ከሀቅ የራቀ ሲሆን ሊቃውንት ጉባኤው ስለጠራው መሄዱ ታውቋል።

Thursday, May 17, 2012

የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ ክፍል የዋልድባን ጉዳይ በተመለከተ የቤተ ክህነቱ አጣሪ ኮሚቴን ሪፖርት ያልዘገበበትን ምክንያት እንዲያብራራ ተጠየቀ

click here to read in PDF
ህዝብ ሆይ ስማ!! ተነስ! ታጠቅ! ዝመት! ዋልድባ ገዳም ተተረማመሰ። እያለ በድረ ገጾቹ ግልጽ ፖለቲካዊ ቅስቀሳ እያደረገ ያለው የመንፈሳዊነት ጭላጩ እንኳ የሌለው ማኅበረ ቅዱሳን በዋልድባ ጉዳይ ከቤተክህነት የተሰጠውን መግለጫ ላለመዘገብ መወሰኑ የቤተክህነቱን ህዝብ ግንኙነት መምሪያ አስቆጣ።
የህዝብ ግንኙነት መምሪያው የሰንበት ማደራጃ መምሪያውን ማኅበረ ቅዱሳን ለምን ዜናውን እዘግባለሁ ካለ በኋላ ባሉት ህጋዊ ሚዲያዎቹ ሁሉ ላለመዘገብ መወሰኑን በተመለከተ ማብራሪያ እንዲሰጥበት በማዘዝ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያው በደብዳቤ ጠይቋል። 
ለዚህ ጥያቄ የራሱን መልስ መስጠት የማይችለው ሰንበት ማደራጃ መምሪያው ጉዳዩ የማህበሩን የሚዲያ ክፍሎች በተመለከተ ይሆናል በሚል ርዕስ ባወጣው ደብዳቤ ለምን ዜናውን ሳትዘግቡ ቀራችሁ የሚል ጥያቄን ጠይቆ ለጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጡበት አዟል። የሁልጊዜውም አላማው የፖለቲካ አየሩ ላይ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ አቧራ ማቡነን የሆነው ማቅ ዋልድባን በተመለከተ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ከፍተኛ ቅስቀሳ እያደረገ ሲሆን ባለፉት 2 ወራት እንኳ ከ20 በላይ የግልጽ ተቃውሞና ህዝብን የማነሳሳት ዘገባዎችን አንዳችም መንፈሳዊ ባህሪ በሌለው መልኩ ማቅረቡ የሚታወስ ነው። እንዲያውም የማህበሩ ብሎጎች በሚያደርጉት ቅስቀሳ ጠብቀውት የነበረውን የአረቦች መነሳሳት አይነት አመጽ ሊያገኙ ባለመቻላቸው ስሜታውያን ህጻናት እንደፈለጉ እንዲቧችሩበት ፈቅዶ ማቅ ባቋቋመው አንድ አድርገን በተሰኘ ብሎግ እኛስ ሞተናል በሚል ርዕስ ምሬቱን መግለጹ አይዘነጋም።

የቅዱስ ሲኖዶስ የስድስተኛ ቀን ውሎ


Click here to read in PDF 
·        ማኅበረ ቅዱሳን የመፍረስ አደጋ ያሰጋዋል
·        ውግዘቱ ሥርአተ ቤተክርስቲያንን ያልተከተለ ነው፤ ይወገዛሉ የተባሉት ግለሰቦች ተጠርተው አልተጠየቁም
·        አባ ሠረቀብርሃንና ዲ/ን በጋሻው ስማቸው ይወገዙ ከተባሉት ውስጥ የለም
ቅዱስ ሲኖዶስ ትናንትና በነበረው የስድስተኛ ቀን ውሎው ሁለት ዋና ዋና ጉዳዮችን ያነሳ ሲሆን የጠዋቱ የማኅበራት ጉዳይ ነው። ከሰዓት በኋላ ደግሞ የተነሳው የሃይማኖት ህጸጽ አለባቸው ስለተባሉ ግለሰቦችና ማኅበራት ጉዳይ ነው።
በጠዋቱ ውሎ በማኅበራት ጉዳይ ላይ የተሰናዳው ጥልቅ ጥናት የቀረበ ሲሆን ጥናቱም በሃይማኖት ጸሎት ላይ ያለውን “ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት” በሚለው መሰረት ጉባኤ የሚለው አንዲት ቤተክርስቲያንን ነውና ሌሎች ማኅበራት አያስፈልጉም። አንዲቷ ቤተክርስቲያን ራስዋ ማኅበር ናትና የሚል ጥቅል ይዘት ያለው ጥናት ቀርቦዋል። ጥናቱ ሁሉንም አባቶች ያስደሰተ ሲሆን፣ አንዳንድ አባቶች ከውሳኔ በፊት ጥናቱ ለሁላችንም ይሰጠንና እናንብበው ብለው ሲጠይቁ አቡነ ቄርሎስ ጥናቱ በጥሩ ሁኔታ ቀርቦአል። ትክክል የምንለውን ውሳኔ መወሰን ነው እንጂ ጽሁፉን እንደገና ወስደን የምናነበው ለምንድን ነው? ብለው በመጠየቃቸው ተባዝቶ ይሰጠን የሚለው ሀሳብ ቀርቶ በጉዳዩ ላይ ዛሬ ለመወሰን ቀጠሮ ተይዟል። ማኅበሯን ትልቅ ስጋት ውስጥ የከተታትም ይኸው ውሳኔ ነው ተብሏል።

Wednesday, May 16, 2012

የሰንበት ማደራጃና መምሪያው ለማኅበረ ቅዱሳን የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ጻፈ

ደብዳቤውን ለማንበብ ይህንን ይጫኑ

  • የ2002 ዓ.ም. ውሳኔ በ10 ቀን ውስጥ እንዲፈጸም ያዛል።
የሰንበት ማደራጀና መምሪያ መምህር ዕንቁ ባሕሪን በዋና ኃላፊነት ካገኘ በኃላ ወሳኝ የሚባሉ አስተዳደሪያዊ ውሳኔዎችን መወሰን ጀምሯል። እንደሰናዖር ግንብ የማይደፈር መስሎት ሲኮፈስ የነበረው ማኅበረ ቅዱሳንም ከሕግ በላይ ሊሆን እንደማይችል በግልጽ የሚረዳበት ዘመን መጥቷል። አመጸኛውና ሕግና ሥርዓትን ጠብቅ ያለኝ ሁሉ መናፍቅ ነው የሚለው ማሕበረ ቅዱሳን ከቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት ውጭ መሆን እንደማይችል የሚገልጸውን ደብዳቤ ለመዋጥ እየተናነቀው ይገኛል።
ከተመሰረትኩ 20 ዓመቴ ነው የሚለውና እንደ 20 ዓመት ጎረምሳ በትዕቢት የተወጣጠረው ማሕበር ቤተክርስትያን እኔ ነኝ የቤተክርስቲያን ዶግማ ቀኖናና ሥርዓት የኔ መተዳደሪያ ደንብ ነው። ሰዎች ወደ ቤተክርስቲያን ሲገቡ ሳይሆን ወደ ማሕበረ ቅዱሳን ሲገቡ ነው የሚድኑትና የቤተክርስቲያን ልጆች ቁጥር እጅግ ጨመረ የሚባለው። ህዝቡ ክርስትና ገባው የሚያባለው አሥራት በኩራቱን ለቤተክርስቲያን መስጠቱን አቁሞ ለማኅበሩ ሲሰጥ ነው። የማኅበረ ቅዱሳን አባል ያልሆነ ሁሉ መናፍቅ ነው። ከሲኖዶሱ በላይ ስለሆንኩ ሲኖዶሱ እኔ ያልኩትን መፈጸም አለበት እያለ እንደ ፊጋ በሬ ቤተክርስቲያንን እያመሰ ቢቆይም ዛሬ ልኩን የሚያውቅበት ቀን መጥቷል።
የማኅበሩ አልታዘዝ ባይነት ወሰን ከማጣቱም በላይ ሥርዓት እንዲይዝ የሚሞክሩትን የቤተክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆች እያዋከበ አላስቆም አላስቀምጥ በማለት ማንም ሊያዘኝ አይችልም በማለት መሬት እርቆት በደመና ላይ እየተንሳፈፈ ቢቆይም አሁን እነርሱም ከሕግ በላይ መሆን እንደማይችል ያሳየና መሬት የሚያስረግጠው ደብዳቤ መጻፉ ተገቢ መሆኑ ታውቋል።

የጉድ ሙዳዩ አቡነ አብርሃም/አዲስ መጽሐፍ/

clicj here to read in PDF
 አቡነ አብርሃምን የሚመለከት የጉድ ሙዳይ የተባለ መጽሐፍ ለህትመት እንደተዘጋጀ በኢሜል የተላከልን መልዕክት አስታወቀ። ይህ የሽፋን ስዕሉንና የመጽሐፉን ከፊል በፒዲኤፍ አካቶ የደረሰን መልዕክት በርካታ ወይ ጉድ የሚያሰኙ ታሪኮችን ያካተተ ሲሆን መጽሀፉ ታተመም አልታተመ የዝግጅት ክፍላችን ወደፊት እንደአስፈላጊነቱ ታሪኩን ለማውጣት ቃል ይገባል።
የሽፋን ስዕሉ እንደሚያስረዳው ሲገለጽ በጊዜው በተባሉ ሰው የተዘጋጀው ይህ መጽሀፍ ርዕሱ የጉድ ሙዳይ ሲባል አቡነ አብርሃምን እንደምናውቃቸው በማለት ደራሲው ከራሱ ጋር ሌሎች በመጽሐፉ ውስጥ ስማቸው የተዘረዘሩ ሰዎችን አንስቷል። የመጽሀፉ ጀርባ እንደሚያስረዳው ዳንኤል ክብረት የተባለ ግለሰብ አቡነ አብርሃምን እንደማውቃቸው ብሎ የጻፈው ጽሁፍ ከ6ወር በፊት እንደደረሳቸውና ይህም ጽሁፍ ሊረሱዋቸው የፈለጉትን ታሪክ ሁሉ ቀስቅሶ ህዝቡ በቀሳጢ ብዕረኛ እንዳይሳሳት ሲሉም መጽሀፉን ለመጻፍ እንደተነሳሱ ገልጸዋል። ሰውየው አንድ ሳይሆን በርካታ ሙዳዮች ያለው ታሪክ ያላቸው ሲሆን ጉድም ለካ የሚሸፈንበት ሙዳይ አለው አስብሎናል።
 በተለይም ከአይነሥውሩ መሪጌታ አስቻለው ጋር የነበራቸው ታሪክና ከጎጃም እስከ ራጉኤል ድረስ የነበራቸውን ሰው አያውቄ ታላቅ ሚስጢር ያስረዳል። “ሀጢአት ዘር ነው ፍሬውን አላጭድም” በሚል አባባላቸው የሚታወቁት አባ አብርሃም ይቺን ቃል ምን ምን ቦታ ላይ እንደሚጠቀሙባት መጽሐፉ በዝርዝር ያስረዳል። ዳንኤል ክብረት ሰውየው መፍቀሬ ማኅበረ ቅዱሳንነታቸውን ተጠቅሞ ለምን የሌላቸውን ሰብዕና ለመገንባት ፈለገ የሚለው ጥያቄ እንዳለ ሆኖ አባ አብርሃም በሚመለከት ተዳፍኖ የነበረውን ስሜት ቀስቅሶ የአባ አብርሃምን እውነተኛ ታሪክ እንድናውቅ በር ስለከፈተልን ተደንቀናል።

ዜና ቤተክርስቲያን በ«ቀሲስ» ዶ/ር መስፍን ላይ «የጤና ዶ/ሩ ከክህነታቸው ተሻሩ» በሚል ርእስ ዘገባ አወጣ


ምንጭ፦ አባ ሰላማ
· «ዶ/ሩ የማኅበረ ቅዱሳን ቀንደኛ አባል፣ … በሥራ  ድክመትና ዛሬ መንግሥት በአሸባሪነት የፈረጃቸውን ግለሰቦች በድርጅቱ ውስጥ በመሰግሰጋቸው ተነቅቶባቸው የተባረሩ ናቸው» ብሏል
·    ማኅበረ ቅዱሳንን በሰይጣን መስሎታል
  • የዘገባው ሙሉ ቃል ከነትንታኔው ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል
«ዶ/ር መስፍን ተገኝ የተባሉት የማኅበረ ቅዱሳን ቀንደኛ አባል ያለ ሀገረ ስብከቱ ሊቀ  ጳጳስ ፈቃድ በሰሜን አሜሪካ ባሉ ስቴቶች በመዘዋወር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም ባደረጉት ኢ-ቀኖናዊ እንቅስቃሴና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ባልጠበቀ ሁኔታ አባቶችን እርስ በርስ የሚያጣላና የሚከፋፍል፤ በማለት የታገዱበትንና ከዚህ ቀደም ድረገጻችን አውጥቶት የነበረውን ደብዳቤ አትሞታል።«ዶ/ር መስፍን ተገኝ ቀደም ሲል በኃላፊነት ይሠሩበት ከነበረው ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ቢሮ በሥራ  ድክመትና ዛሬ መንግሥት በአሸባሪነት የፈረጃቸውን ግለሰቦች በድርጅቱ ውስጥ በመሰግሰጋቸው ተነቅቶባቸው የተባረሩ ናቸው፡፡

ምእመናንንም ለአድማ የሚያነሳሳ ትምህርት የሰጡ መሆናቸው በማስረጃ ስለተረጋገጠባቸው እንዲመከሩና በንስሐ እንዲመለሱ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል የሰሜን አሜሪካና የካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ተደጋጋሚ ጥሪ ቢያደርጉላቸው ጥሪውን በመናቃቸው በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 6 በቁጥር 224 ሦስተኛ ረስጠብ 22ኛው ድንጋጌ መሠረት ሊቀ ጳጳሱ ሥልጣነ ክህነታቸውን ሽረውታል፤ ከክህነታዊ አገልግሎትም አግደዋቸዋል፡፡»
«ዶ/ር መስፍን ከተጠቀሰው መሥሪያ ቤት ከተባበሩ በኋላም ለለጋሽ ድርጅቶች የተሳሳተ ኢንፎርሜሽን በመስጠት በብፁዕ ወቅድስ ፓትርያርኩ ጥረት ቤተ ክርስቲያናችን በሥራ ውጤት ከአሜሪካ መንግሥት ሽልማት ያገኘችበት የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ቢሮ እንዲዘጋ በማስደረግ ሕሙማኑንም ሆነ የቢሮው ሠራተኞችን የበደሉ ከመሆናቸውም በላይ በሙያቸው የጀመሩት ሥራ አልሳካ ሲላቸው ‹‹ላም ካልዋለበት ኩበት ለቀማ›› እንዲሉ ፈተና የሌለበት መስሎአቸው የበለጠ ፈተና ወደአለበት ወደዚህ መንፈሳዊ ተግባር አምርተው በጅምራቸው ለዚህ ዓይነቱ መንፈሳዊ አደጋ የተጋለጡ ግለሰብ ናቸው፡፡» ብሏል። 

Tuesday, May 15, 2012

የቅዱስ ሲኖዶስ የዛሬ ከሰዓት ውሎ

Click here to read in PDF
  • የዜና ቤተክርስቲያን ጋዜጣ ጉዳይ ወደ ኮሚቴ ተላለፈ
ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬ ከሰዓት ውሎው የዜና ቤተክርስቲያናት ጋዜጣን ጉዳይ እንዴት እንዝጋው በሚል የተነጋገረ ሲሆን የአቡነ ሉቃስ የአቡነ ዲዮስቆሮስ የአቡነ አብርሀምና የአቡነ ሳሙኤል የይወገዙልን ፉከራ ገደብ አጥቶ እንደነበር ተነግሮዋል። በአንድ ወቅት አንድ ብጹዕ አባት ማኅበረ ቅዱሳንን የሚደግፍ የጀርባ ቁስል ያለበት ብቻ ነው ብለው እንደተናገሩት የጀርባ ቁስላቸውን እንዲያኩላቸው በማሰብ የማኅበረ ቅዱሳን ደጋፊ የሆኑት እነዚህ ጳጳሳት በምሳው እረፍት ከማህበሩ ሰዎች በተሰጣቸው መመሪያ መሰረት የይወገዙልን  ጥያቄውን አጠንክረው አቅርበዋል።
 በዚህ ሰበር አጀንዳ የተሰላቹት ቅዱሳን አባቶች ወይ ተጠርተው ይጠየቁ አሊያም ደግሞ አንድ ውሳኔ ይደረግ ብለው በጠየቁት መሰረት ቅዱስነታቸው የብጹአን አባቶች ፍላጉት ይሄ ከሆኑ አዘጋጆቹ ይግቡ ብለው ነበር። ነገር ግን አራት ሊቃነ ጳጳሳት እነርሱ ከገቡ እኛ አንቀመጥም ብለው ብድግ ስላሉ ይግቡ የሚለው ትዕዛዝ እንደገና ሊታጠፍ ችሏል።