Thursday, May 17, 2012

የቅዱስ ሲኖዶስ የስድስተኛ ቀን ውሎ


Click here to read in PDF 
·        ማኅበረ ቅዱሳን የመፍረስ አደጋ ያሰጋዋል
·        ውግዘቱ ሥርአተ ቤተክርስቲያንን ያልተከተለ ነው፤ ይወገዛሉ የተባሉት ግለሰቦች ተጠርተው አልተጠየቁም
·        አባ ሠረቀብርሃንና ዲ/ን በጋሻው ስማቸው ይወገዙ ከተባሉት ውስጥ የለም
ቅዱስ ሲኖዶስ ትናንትና በነበረው የስድስተኛ ቀን ውሎው ሁለት ዋና ዋና ጉዳዮችን ያነሳ ሲሆን የጠዋቱ የማኅበራት ጉዳይ ነው። ከሰዓት በኋላ ደግሞ የተነሳው የሃይማኖት ህጸጽ አለባቸው ስለተባሉ ግለሰቦችና ማኅበራት ጉዳይ ነው።
በጠዋቱ ውሎ በማኅበራት ጉዳይ ላይ የተሰናዳው ጥልቅ ጥናት የቀረበ ሲሆን ጥናቱም በሃይማኖት ጸሎት ላይ ያለውን “ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት” በሚለው መሰረት ጉባኤ የሚለው አንዲት ቤተክርስቲያንን ነውና ሌሎች ማኅበራት አያስፈልጉም። አንዲቷ ቤተክርስቲያን ራስዋ ማኅበር ናትና የሚል ጥቅል ይዘት ያለው ጥናት ቀርቦዋል። ጥናቱ ሁሉንም አባቶች ያስደሰተ ሲሆን፣ አንዳንድ አባቶች ከውሳኔ በፊት ጥናቱ ለሁላችንም ይሰጠንና እናንብበው ብለው ሲጠይቁ አቡነ ቄርሎስ ጥናቱ በጥሩ ሁኔታ ቀርቦአል። ትክክል የምንለውን ውሳኔ መወሰን ነው እንጂ ጽሁፉን እንደገና ወስደን የምናነበው ለምንድን ነው? ብለው በመጠየቃቸው ተባዝቶ ይሰጠን የሚለው ሀሳብ ቀርቶ በጉዳዩ ላይ ዛሬ ለመወሰን ቀጠሮ ተይዟል። ማኅበሯን ትልቅ ስጋት ውስጥ የከተታትም ይኸው ውሳኔ ነው ተብሏል።

ማኅበራት እስካሁን ባላቸው አሰራርና ባደረጉት እንቅስቃሴ ራሳቸውን እንጂ ቤተክርስቲያንን የጠቀሙበት ሁኔታ ያን ያህል ነው። ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳታቸው አመዝኖ እንደታየ ያመለከተው ጥናቱ፣ እንዲያውም በአባቶች መካከል የሚነሱትን መጠነኛ የሀሳብ ልዩነቶች በማስፋትና በራሳቸው መንገድ ነገሩን በመጠምዘዝ እየተጫወቱት ያለው አፍራሽ ሚና ይበልጣል ማለቱ ተነግሮአል። ስለዚህ ከዚህ የከፋ ጉዳት ሳያስከትሉ በማኅበራት ላይ ውሳኔ መተላለፍ እንዳለበት ግንዛቤ ተወስዷል። የተሻለውም አማራጭ ማኅበራትና ማፍረስ ነው ሲል ጥናቱ የመፍትሔ ሀሳብ አቅርቧል።
ማኅበራትን በተመለከተ የቀረበው ጥናት ድምዳሜው ከአንዲት ቤተክርስቲያን ውጭ ማኅበራት ኣያስፈልጉም የሚል መሆኑን የሰሙት የማኅበረ ቅዱሳን ግልጽ አመራሮችና ጀሌዎቻቸው፣ ትናንትና ከሰዓት በኋላ ግቢውን ወረውት የነበረ መሆኑ ሲታወቅ፣ ገቢ ወጪው ሁሉ ማኅበሩን ሊያፈርስ የመጣ ግብረ ኃይል እየመሰላቸው አይናቸውን ሲያጉረጠርጡበትና ሲደናበሩ መዋላቸውን በስፍራው የነበሩ የአይን እማኞች ተናግረዋል።
በትናንትና የከሰዓት በኋላ ውሎ የሃይማኖት ህጸጽ አለባቸው የተባሉ ግለሰቦችና ማኅበራት ጉዳይ የታየ ሲሆን፣ በጥቅምቱ ሲኖዶስ ስብሰባ ላይ የተወሰነው በተለይ ግለሰቦቹ በህጋዊ መንገድ ተጠርተው እንዲጠየቁ፣ አቋማቸውን እንዲያሳውቁና በዚያ ላይ ተመስርቶ አጣሪ ኮሚቴው የደረሰበትን ድምዳሜ ለቅዱስ ሲኖዶስ ያቀርብና ውሳኔ ይሰጣል የሚል ነበር። እስካሁን ባለን መረጃ ማኅበረ ቅዱሳን ከአባ ሠረቀ ብርሃንና ከሊቀ ካህናት ጌታቸው ዶኒ በስተቀር፣ ይወገዙልኝ ያላቸው ግለሰቦች በሙሉ ከሊቃውንት ጉባኤ ጥሪ እንዳልተደረገላቸውና ቀርበው የሰጡት ሐሳብ እንደሌለ ታውቋል። ስለሆነም ጳጳሳቱ በዚህ መንገድ በማኅበረ ቅዱሳን ተቀነባብሮ የቀረበላቸውን ክስ ብቻ ተቀብለው ግለሰቦቹን ሳያነጋግሩና ሀሳባቸውን ሳይጠይቁ ውግዘት ቢያስተላልፉ ይህችን ታላቅ ቤተክርስቲያን ትልቅ ውርደት ላይ የሚጥልና ራሳቸውንም የሚያስገምት ውሳኔ እንዳስተላለፉ ይቆጠራል የሚሉ ብዙዎች ናቸው። ምክንያቱም በሃይማኖት ሕጸጽ የተጠረጠረ ሰው ከመወገዙ በፊት ተጠርቶ ሊጠየቅና በእርሱ ሐሳብ ላይ ተመስርቶና ህገ ቤተክርስቲያንን መርምሮ ውሳኔ መስጠት ተገቢና ተቀባይነት ያለው አሰራር ነው።
ቤተክርስቲያን የተሳሳቱ ካሉም ቅድሚያው መስጠት ያለባት መክሮ ለመመለስ እንጂ ለማውገዝ እንዳልሆነ የኖረ የቤተክርስታያኒቱ አቋም ነው። ከዚህ ቀደም ቅዱስ ፓትርያርኩ የጻፉትና በመላው ኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የበተኑት ደብዳቤም ይህንኑ የሚያስረዳ ነው። ይህን መንፈሳዊ አሰራር ወደጎን በማለት በማኅበረ ቅዱሳን ግፊት የከሳሽን አቤቱታ ብቻ ሰምቶና ተከሳሽን ሳያነጋግር ህግን ባልተከተለ መንገድ ማውገዝ ፈጽሞ ተቀባይነት እንደሌለው አእምሮ ያለቸው አባቶችና ምእመናን ሁሉ የሚገነዘቡት እውነት ነው። በቤተክርስቲያን ላይ የሚያስከትለውም አደጋ ዛሬ ባይታያቸውም ከፍተኛ መሆኑ አይጠረጠርም። 
ጳጰሳቱ የውግዘቱን ጉዳይ ለማጣደፍ የተነሱበት ዋናው ምክንያት በዜና ቤተክርስቲያን የቀረበባቸውን ፍጹም አለማዊነት የተሞላ ሕይወት ለመሸፋፈንና ስብሰባውን አቅጣጫ ለማስለወጥ እንደሆነ ተገምቷል። አንዳንድ አላዋቂዎች ሃይማኖትንና ምግባርን ለያይተው ከምግባር ህጸጽ የሃይማኖት ሕጸጽ ይከፋል ይላሉ። ግን ፍጹም ስህተት ነው። ምግባር የሚበላሸው ሃይማኖት ሲበላሽ ነው። ከቀና ሃይማኖት በጎ ምግባር ይገኛል። ህጹጽ ሃይማኖት ግን ብልሹ ምግባር እንጂ በጎ ምግባር አይገኝበትም። በዜና ቤተክርስቲያን የተዘረዘረውና ያልተዘረዘረውም በብዙዎች ዘንድ የታወቀው እንደዚያ ያለ ከጳጳሳት የማይጠበቅ ምግባረ ብልሹነት ከቀና ሃይማኖት እንደማይገኝ የታወቀ ነው። የቀና ሃይማኖት በጎ ምግባርም ይከተለዋልና። እንዲህ ባለ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ጳጳሳት ሳይጠይቁና ሳይመረምሩ ሌላውን ለማውገዝ ብቃትም ሞራልም የላቸውም። ጳጳስ ስለሆን ብቻ እንችላለን ካሉም ውግዘቱ ዖፈገዝት ከመሆን አያልፍም ይላሉ እነዚሁ አስተያየታቸውን የሚሰጡ ወገኖች።  
ይህ በእንዲህ እንዳለ ማኅበረ ቅዱሳን ከሌሎቹ ይልቅ እነርሱ ቢወገዙልኝ የሚላቸው አባ ሠረቀብርሃንና ዲ/ን በጋሻው በውግዘቱ ላይ ስማቸው እንዳልተካተተ ታውቋል። ሲኖዶሱ በዛሬው ውሎው በእነዚህ ሁለት ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።


2 comments:

  1. ቅዱስ ሲኖዶስ በሃይማኖትና በቀኖና ጉዳዮች አይሳሳትም፣ በአስተዳደር ጉዳዩች ግን ስሕተቶችን ያርማል፣ መተዳደሪያዎችን ያሻሽላል፡፡

    የማኅበረ ቅዱሳን መተዳደሪያ ደንብ ያለ አግባብ የጸደቀ አባቶች በየዋሐት በደርግ ዘመን በየዩኒቨርስቲው በፖለቲካና በጥላቻ የተወሰዱ ወጣቶችን ወደ ቤተ ክርስቲያን ለማምጣት ብለው የሠሩት አስተዳደራዊ ውሳኔ ሲሆን አሁን ሊታረምና በሰንበት ትምህርት ቤቶች መተዳደሪያ ሊተካ ይገባዋል፡፡

    1. ቅዱስ ሲኖዶስ ለአንዲት ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ቃለ ዓዋዲንና ለወጣቶች ሰንበት ትምህርት ቤትና የማኅበራት መተዳደሪያን ደንብን መስጠቱ ሊስተካከል ይገባል፡፡ ወጣቱ በማንኛው ይካተት (ከቤ/ክ ውጭ በማኅበር ወይስ ቤ/ክ ውስጥ በሰንበት ት/ቤት)ስለዚህ ሁሉም ምእመናን በቃለ ዓዋዲ የሚተዳደሩ ሲሆን ወጣቶች በሰንበት ትምህርት ቤት ብቻ ይታቀፋሉ፡፡ መተዳደሪያቸው የአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤት መተዳደሪያ ይሆናል፡፡
    2. የማኅበራት አደረጃጀት በኦሬንታል ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ፈጽሞ የለም በሌሎችም አብያተ ክርስቲያናት ያልተለመደ ሕገ ወጥ አሠራር ነው፡፡
    3. ማቅ የራሱን አባላት ለማበራከት ከቤተ ክርስቲያን አባላት አባላትን ይመርጣል፣ ጉዳዩ ምንድን ነው ሌላ ቤተ ክርስቲያን ለመመሥረት ነው
    4. የማቅ ንብረቶች አዛዥ የላቸውም፣ ሂሳቡ ተቆጣጣሪ የለውም፣
    5. የማኅበረ ቅዱሳን አመራር ሲመረቱ መሥፈርቱን ቅዱስ ሲኖዶስ አያውቀውም
    6. ቅዱስ ሲኖዶስ ደንቡን አጸደቀ እንጅ የአባልነት ፎርም አላጸደቀም
    7. አባላት በማኅበረ ቅዱሳን ውስጥ ለስንት ጊዜ አባል እንደሚሆን ድንጋጌ የለም
    8. ማኅበረ ቅዱሳን ከሰበካ ጉባኤ፣ ከወረዳ፣ ከሀገረ ስብከት እና ከጠቅላይ ቤ/ክ በላይ ገንዘብ ይሰበስባል
    9. የማኅበረ ቅዱሳን አመራር አባላት ከሰባ በመቶ በላይ ፖለቲከኛዎች ናቸው
    10. ማኅበረ ቅዱሳን ከሙስሊም አሸባሪዎች ጋር ከፍኛ ተመሳሳይነት አለው
    11. ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክህነትና ለሊቃውንት ከፍተኛ ጥላቻ አለበት
    12. ማኅበረ ቅዱሳን መተዳደሪያ ከቃለ ዐዋዲ ይበልጣል
    13. ማኅበረ ቅዱሳን ለበርካታ ሰንበት ትምህረት ወጣቶች መዳከም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው
    14. የማኅበረ ቅዱሳን መተዳደሪያ ከቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ አደረጃጀት ጋር ከፍተኛ ተቃርኖ አለው
    15. ማኅበረ ቅዱሳን የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችን እየመረጠ የራሱ አባል ያደርጋል
    16. ማኅበረ ቅዱሳን ከቤተ ክርስቲያን ውጭ (ከያሬዳዊ መዘምራን መሪጌቶች፣ ለሰንበት ትምህርት ቤት) ለመጀመሪያ ጊዜ የመዘምራን ኳየር ያዋቀረ ሕገ ወጥ የፕሮቴስታንት ተምሳሌት
    17. ማኅበረ ቅዱሳን ከቤተ ክርስቲያን ጸሎት ይልቅ ለራሱ የቡድን ጸሎት ቅድሚያ ይሰጣል
    18. የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ሳይምሩና ሳይመረመሩ ሹመትን ይቀበላሉ
    19. ማኅበረ ቅዱሳን ሳይፈቀድለት በበጎ ፈቃድ ማገልገል ሲገባው እጅግ ከፍኛ ደመወዝ እየከፈለ ሰዎችን ያሠራል
    20. ማኅበረ ቅዱሳን ሳይፈቀድለት ከሦስተኛ ወገን ጋር ውል ይገባል በቅርቡ የዐራት ሚሊያን ብር የኮንስትራክሽን ውል ገብቷል፣ ጉዳዩን ጠቅላይ ቤጸ ክህነት አያውቀውም
    21. ማኅበረ ቅዱሳን በርካታ ትናንሽ ማኅበራትን አጥፍቷል፣ ጠቅልሏል፣ ሥራቸውን ወርሷል
    22. ማኅበረ ቅዱሳን ከዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ውጭ በርካታ ነጋዴዎችን፣ የመንግሥት ሠራተኞችን፣ አባላቱ እንዲያደርግ ማን ፈቀደለት (ዕውነተኛ ከሆነ ለምን ከማኅበር ይልቅ ለቤ/ክ አገልጋይ አያደርጋቸውም)
    23. የማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ ባለቤት ማነው
    24. ማኅበረ ቅዱሳን በከፍተኛ ደረጃ የግለሰቦችን መረጃ ይሰበስባል፣ ትውልዳቸውን ያጠናል…. ለምን
    25. የማኅበረ ቅዱሳን የመረጃ መረቦች ግልጽነት የሌላቸው እና የዋናው አንጃ ውክልና ያላቸው የማኅበረ ቅዱሳን የፖለቲካና ዓለማዊ ጥላቻ ማስተላለፊያ ድረ ገጾቹ የማኅበረ ቅዱሳን ትክክለኛ መልክ ሲያሳዩ ይፋዊ ሆነው የእኔ የሚላቸው ደግሞ ማኅበረ ቅዱሳንን በጭምብል ያሳያሉ
    26. ማኅበረ ቅዱሳን እጅግ ዘርፈ ብዙ በሆነና በጣም በተስፋፋ የንግድና የልመና፣ የፕሮጀክት መረብ ለምን ኖረው
    27. ማኅበረ ቅዱሳን ቅዱስ ሲኖዶስ በጀት መድቦ፣ መምህራን ቀጥሮ በሚያቋቁማቸው ገዳማትና፣ አብነት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተጨማሪና መጠነኛ ድጎማ እየሰጠ መምህራኑንና ተማሪዎቹን አባላት ወይም ደጋፊ ያደርጋል፡፡ ይህም ማለት በሰው ቤት ውስጥ ለሠራተኛዎ ተጨማሪ ብር ባለ ድርብ ተልዕኮ ማድረግ ነው
    28. ማኅበረ ቅዱሳን በርካታ ማኀበራትን በአርአያው ፈጥሯል ለምሳሌ (ደጆችሽ አይዘጉ፣ የቴዎሎጅ ምሩቃን ማኅበር፣ የአቡነ ሐራ ማኅበር፣ ማኅበረ ሰላም፣ … )
    29. ማኅበረ ቅዱሳን ለብዙ አባላቱ ከፍተኛ የኑሮ ድጎማን በቤ/ክ ስም ሰጥቷ፣ መኪና ገዝተዋል፣ ቤት ሠርተዋል…
    30. ማኅበረ ቅዱሳን ሁለት የመንደር ቡድኖች አሉ የጎንደሮች ቡድን አቡነ መርቆሬዮስን ፓትርያርክ ለማድረግ የሚንቀሳቀስ፣ እና የሸዋ ቡድን የሸዋ ፓትርያርክ ለመሾም የሚንቀሳቀስ ሌላው አጫፋሪ ነው፡፡

    ተጨማሪ ሠላሣ ጉዳዩችን በቀጣይ ይጠብቁ

    ReplyDelete
  2. ቅዱስ ሲኖዶስ በሃይማኖትና በቀኖና ጉዳዮች አይሳሳትም፣ በአስተዳደር ጉዳዩች ግን ስሕተቶችን ያርማል፣ መተዳደሪያዎችን ያሻሽላል፡፡

    የማኅበረ ቅዱሳን መተዳደሪያ ደንብ ያለ አግባብ የጸደቀ አባቶች በየዋሐት በደርግ ዘመን በየዩኒቨርስቲው በፖለቲካና በጥላቻ የተወሰዱ ወጣቶችን ወደ ቤተ ክርስቲያን ለማምጣት ብለው የሠሩት አስተዳደራዊ ውሳኔ ሲሆን አሁን ሊታረምና በሰንበት ትምህርት ቤቶች መተዳደሪያ ሊተካ ይገባዋል፡፡

    1. ቅዱስ ሲኖዶስ ለአንዲት ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ቃለ ዓዋዲንና ለወጣቶች ሰንበት ትምህርት ቤትና የማኅበራት መተዳደሪያን ደንብን መስጠቱ ሊስተካከል ይገባል፡፡ ወጣቱ በማንኛው ይካተት (ከቤ/ክ ውጭ በማኅበር ወይስ ቤ/ክ ውስጥ በሰንበት ት/ቤት)ስለዚህ ሁሉም ምእመናን በቃለ ዓዋዲ የሚተዳደሩ ሲሆን ወጣቶች በሰንበት ትምህርት ቤት ብቻ ይታቀፋሉ፡፡ መተዳደሪያቸው የአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤት መተዳደሪያ ይሆናል፡፡
    2. የማኅበራት አደረጃጀት በኦሬንታል ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ፈጽሞ የለም በሌሎችም አብያተ ክርስቲያናት ያልተለመደ ሕገ ወጥ አሠራር ነው፡፡
    3. ማቅ የራሱን አባላት ለማበራከት ከቤተ ክርስቲያን አባላት አባላትን ይመርጣል፣ ጉዳዩ ምንድን ነው ሌላ ቤተ ክርስቲያን ለመመሥረት ነው
    4. የማቅ ንብረቶች አዛዥ የላቸውም፣ ሂሳቡ ተቆጣጣሪ የለውም፣
    5. የማኅበረ ቅዱሳን አመራር ሲመረቱ መሥፈርቱን ቅዱስ ሲኖዶስ አያውቀውም
    6. ቅዱስ ሲኖዶስ ደንቡን አጸደቀ እንጅ የአባልነት ፎርም አላጸደቀም
    7. አባላት በማኅበረ ቅዱሳን ውስጥ ለስንት ጊዜ አባል እንደሚሆን ድንጋጌ የለም
    8. ማኅበረ ቅዱሳን ከሰበካ ጉባኤ፣ ከወረዳ፣ ከሀገረ ስብከት እና ከጠቅላይ ቤ/ክ በላይ ገንዘብ ይሰበስባል
    9. የማኅበረ ቅዱሳን አመራር አባላት ከሰባ በመቶ በላይ ፖለቲከኛዎች ናቸው
    10. ማኅበረ ቅዱሳን ከሙስሊም አሸባሪዎች ጋር ከፍኛ ተመሳሳይነት አለው
    11. ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክህነትና ለሊቃውንት ከፍተኛ ጥላቻ አለበት
    12. ማኅበረ ቅዱሳን መተዳደሪያ ከቃለ ዐዋዲ ይበልጣል
    13. ማኅበረ ቅዱሳን ለበርካታ ሰንበት ትምህረት ወጣቶች መዳከም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው
    14. የማኅበረ ቅዱሳን መተዳደሪያ ከቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ አደረጃጀት ጋር ከፍተኛ ተቃርኖ አለው
    15. ማኅበረ ቅዱሳን የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችን እየመረጠ የራሱ አባል ያደርጋል
    16. ማኅበረ ቅዱሳን ከቤተ ክርስቲያን ውጭ (ከያሬዳዊ መዘምራን መሪጌቶች፣ ለሰንበት ትምህርት ቤት) ለመጀመሪያ ጊዜ የመዘምራን ኳየር ያዋቀረ ሕገ ወጥ የፕሮቴስታንት ተምሳሌት
    17. ማኅበረ ቅዱሳን ከቤተ ክርስቲያን ጸሎት ይልቅ ለራሱ የቡድን ጸሎት ቅድሚያ ይሰጣል
    18. የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ሳይምሩና ሳይመረመሩ ሹመትን ይቀበላሉ
    19. ማኅበረ ቅዱሳን ሳይፈቀድለት በበጎ ፈቃድ ማገልገል ሲገባው እጅግ ከፍኛ ደመወዝ እየከፈለ ሰዎችን ያሠራል
    20. ማኅበረ ቅዱሳን ሳይፈቀድለት ከሦስተኛ ወገን ጋር ውል ይገባል በቅርቡ የዐራት ሚሊያን ብር የኮንስትራክሽን ውል ገብቷል፣ ጉዳዩን ጠቅላይ ቤጸ ክህነት አያውቀውም
    21. ማኅበረ ቅዱሳን በርካታ ትናንሽ ማኅበራትን አጥፍቷል፣ ጠቅልሏል፣ ሥራቸውን ወርሷል
    22. ማኅበረ ቅዱሳን ከዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ውጭ በርካታ ነጋዴዎችን፣ የመንግሥት ሠራተኞችን፣ አባላቱ እንዲያደርግ ማን ፈቀደለት (ዕውነተኛ ከሆነ ለምን ከማኅበር ይልቅ ለቤ/ክ አገልጋይ አያደርጋቸውም)
    23. የማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ ባለቤት ማነው
    24. ማኅበረ ቅዱሳን በከፍተኛ ደረጃ የግለሰቦችን መረጃ ይሰበስባል፣ ትውልዳቸውን ያጠናል…. ለምን
    25. የማኅበረ ቅዱሳን የመረጃ መረቦች ግልጽነት የሌላቸው እና የዋናው አንጃ ውክልና ያላቸው የማኅበረ ቅዱሳን የፖለቲካና ዓለማዊ ጥላቻ ማስተላለፊያ ድረ ገጾቹ የማኅበረ ቅዱሳን ትክክለኛ መልክ ሲያሳዩ ይፋዊ ሆነው የእኔ የሚላቸው ደግሞ ማኅበረ ቅዱሳንን በጭምብል ያሳያሉ
    26. ማኅበረ ቅዱሳን እጅግ ዘርፈ ብዙ በሆነና በጣም በተስፋፋ የንግድና የልመና፣ የፕሮጀክት መረብ ለምን ኖረው
    27. ማኅበረ ቅዱሳን ቅዱስ ሲኖዶስ በጀት መድቦ፣ መምህራን ቀጥሮ በሚያቋቁማቸው ገዳማትና፣ አብነት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተጨማሪና መጠነኛ ድጎማ እየሰጠ መምህራኑንና ተማሪዎቹን አባላት ወይም ደጋፊ ያደርጋል፡፡ ይህም ማለት በሰው ቤት ውስጥ ለሠራተኛዎ ተጨማሪ ብር ባለ ድርብ ተልዕኮ ማድረግ ነው
    28. ማኅበረ ቅዱሳን በርካታ ማኀበራትን በአርአያው ፈጥሯል ለምሳሌ (ደጆችሽ አይዘጉ፣ የቴዎሎጅ ምሩቃን ማኅበር፣ የአቡነ ሐራ ማኅበር፣ ማኅበረ ሰላም፣ … )
    29. ማኅበረ ቅዱሳን ለብዙ አባላቱ ከፍተኛ የኑሮ ድጎማን በቤ/ክ ስም ሰጥቷ፣ መኪና ገዝተዋል፣ ቤት ሠርተዋል…
    30. ማኅበረ ቅዱሳን ሁለት የመንደር ቡድኖች አሉ የጎንደሮች ቡድን አቡነ መርቆሬዮስን ፓትርያርክ ለማድረግ የሚንቀሳቀስ፣ እና የሸዋ ቡድን የሸዋ ፓትርያርክ ለመሾም የሚንቀሳቀስ ሌላው አጫፋሪ ነው፡፡

    ተጨማሪ ሠላሣ ጉዳዩችን በቀጣይ ይጠብቁ

    ReplyDelete