ከደቡብ
አፍሪካ
ይድረስ...........ይድረስ........ይድረስ፦ከጥቅም ጋር ሳይሆን ስለእውነት ለምትሰሩ አባቶች፤ ለዘር ሳይሆን ለእምነታችሁ ለቆማችሁ አባቶች፤ ከሀሰተኞች ጋር ሳይሆን ከእውነት ፊት ለምትቆሙ አባቶች። >> መቼም (ጉድ ሳይሰማ መስከረም ኣይጠባም)>> የተባለው በዚህ ባለንበት በደቡብ አፍሪካ በተግባር መተርጎም ከጀመረ ዘመናትን አስቆጥሮኣል። ይሁንና (የአሁኑ ይባስ) ብሎ በጣም የሚያስግርሙና አረ ወዴት እንሂድ?..... ወደ ማንስ አቤት እንበል?..... የሚያሰኙና፡ እንዲሁም ቤተክርስቲያኗ የማናት?......... ባለቤቷስ ማነው?......... መንፈስ ቅዱስ ወይስ የአንድ ፓለቲካ ድርጅት? የቤተክርስቲያኗ ባለቤቶችስ በውስጧ የሚያገለግሉና የሚገለገሉ አማኞች ወይስ የገቢዋ ተጠቃሚ የሆኑ (የሆነ)ግለሰብ? መልሱን በጽሑፍ ሳይሆን በተግባር ለሚመልስ አውነተኛ እረኛ ስለ በጎቹ (ምእመናን)ለሚገደው ሁሉ ትቼዋለሁ።
መቼም ከላይ ለተዘረዘሩት አጅግ ጥቂት፡ ነገር ግን መሰረታዊ ለሆኑ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ጊዜያችሁን እንደማትቆጥቡ በመተማመን ወደ ተነሳሁበትና፡ ለአንድ ሙሉ አመት የምእመናን ጭንቀትና መወያያ ሆኖ ከመቆየቱም ባሻገር አጅግ አስገራሚና ለሰሚ ጉድ ያሰኝውን በስላሴ ስም በተሰየመው ቤተክርስቲያን እየተከናወነ ስለ አለው ፡ እቃቃ_ እቃቃ ልበለው?........ ወይም አንቆቅልሽ?....... አሊያም . . . . . .
. ብቻ ለኔ የሚመጥነው ቃላት ያላገኘሁለትንና፦ የብዙዎችን ልብ ክፉኛ ያሳዘነውን አስገራሚ ታሪክ ባጭሩ፡ በማስተዋል ለመጓዝና አውነቱ ምን አንደሆን አውቆ ለህሊና ዳኝነት ይረዳችሁ ዘንድ ብሎም ስለቤተክርስቲያኗ የሚገዳቸው አባቶች አፋጣኝ መፍትሄ እንዲፈልጉልን ይረዳ ዘንድ ከዚህ አንደሚከተለው በዝርዝር የታዘብኩትንና በአማኝነቴ ውስጤን የጎዳውን ለማሳየት አሞክራለሁ።

