Wednesday, October 24, 2012

ሲኖዶሱና ሁለተኛ ቀኑ

Read in PDf:day 2
በዛሬው እለት በተደረገው የሲኖዶስ ስብሰባ የተነሱት ሁለት አጀንዳዎች ብቻ ሲሆኑ እነርሱም የቤቶች አስተዳደር ጉዳይ እና የእርቁ ጉዳይ ነው፡፡ እርቁን በተመለከተ አቡነ መርቆሬዎስ የላኩት ደብዳቤ የተነበበ ሲሆን ቅዱስነታቸው በደብዳቤው መጥታችሁ ፊት ለፊት እንነጋገር የሚል መልእክት ያለው ነው፡፡ አስታራቂ ኮሚቴዎቹ ቀርበው ስለእርቁ ሁኔታ ያስረዱ ሲሆን መጥታችሁ እንነጋገር የሚለውን የአቡነ መርቆሬዎስ መልእክት ተመርኩዘው አቡነ ናትናኤል የመሄድ ፍላጉት ቢሳያዩም ሲኖዶሱ ግን እርስዋ አይሄዱም ከዚህ በፊት የጀመሩት እነ አቡነ ገሪማ ናቸው መሄድ ያለባቸው ሲል ወስኗል፡፡
እርቁን በተመለከተ የተንሸራሸሩ በርካታ ጉዳዮች ቢኖሩም ለዕርቁ ሲኬት ሲባል እናልፈዋለን፡፡ የቤቶች አስተዳዳርን በተመለከተም የጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል ስራ አስኪጁ አቶ ተስፋዬ ስለአጠቃላይ ሁኔታ ቀርቦ አስረድቷል፡፡

No comments:

Post a Comment