Monday, August 27, 2012

የክብረ መንግስት ከተማ የማኅበረ ቅዱሳን ወኪሎች ቅብጠትና የመንግስት ምላሽ


 Click here to read inPDF: kebbremenegeste kidanemihret
(አውደ ምህረት፤ ሰኞ ነሐሴ 21 2004 ዓ.ም. /awdemihret.blogspot.com// awdemihret.wordpress.com) ቅዱስነታቸው ካረፉ በኃላ ጊዜው የኛ ነው በማለት የሚሆኑትን ያጡት የማኅበረ ቅዱሳን ሰዎች በማን አለብኝነት ስሜት ያለ ሊቀጳጳስ ትዕዛዝ በየካቲት ወር እንጂ በነሐሴ 16 ቀን ነግሳ የማታውቀዎን የክብረ መንግስት ኪዳነምህረትን በማንገሳቸው እና ሀገሪቱ ብሔራዊ ሀዘን አውጃ ሳለ ባንዲራ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ በማድረጋቸው ከመንግስት ኃላፊዎች ጋር መጋጨታቸው ተሰማ።
በአካባቢው በተሰራው ደንብ እና የገጠር አብያተ ክርስቲያናትም የንግስ በዓል እንዲያከብሩ በተደረገው መሰረት የነሐሴ ፍልሰታ ንግስ የጨንቢ ኪዳነምህረት ተራ መሆኑን እያወቁ እና ከክብረ መንግስት ካህናት ካልሄዱም በቀር ማንገስ እንደማይቻል እየተረዱ የጨንቢ ኪዳነ ምህረትን ንግስ ወደጎን ብለው የክብረ መንግስት ኪዳነ ምህረትን አንግሰዋል:: በንግሱ ዕለትም ባንዲራ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ አድርገዋል፡፡
የክልሉ መንግስት ባለስልጣናትም የጉዳዩ ዋና ተዋናይ የነበሩትን እና የየካቲት ኪዳነ ምህረት ዕለት ተከስቶ በነበረው ብጥብጥ ታስረው የነበሩትን እነ ሊቀስዩማን ልሳነወርቅ ሁንዴን ጠርተው እንዲጠየቁ ያደረጉ ሲሆን ያለ ሊቀ ጳጳስ ፈቃድ በቤተክርስቲያኒቱ ንግስ እንዲነግስ ያደረጉበትን ምክንያት እና ባንዲራ ከፍ አድርገው ያወለበለቡበትን የደስታቸውን ምንጭ በአግባቡ ማስረዳት ሳይችሉ ቀርተዋል፡፡ ከዚህም የተነሳ በከባድ ማስጠቀቂያ መታለፋቸውን ምንጮቻችን አስታውቀዋል።
ይህ ሁኔታ ያስደነገጣቸው ሊቀስዩማን ልሳነ ወርቅ ሁንዴ በጠቀላ ሚኒስቴሩ ሞት ምክንያት በትናንትናው ዕለት በነበረው የአደባባይ ሀዘን ሰንበት ተማሪ አሰልፈው የወጡ ሲሆን ንግግር ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ቢያደርጉም ሳይፈቀድላቸው ቀርቷል፡፡ የእሳቸው ሁኔታ ተጣርቶ እስኪታወቅም በማንኛወም ሁኔታ ላይ ቤተክርስቲያንን ወክለው ንግግር ማድረግ እንደማይችሉ ተነግሯቸዋል፡፡ ለቀስዩማኑ ከነበራቸው ሀላፊነት በህጋዊ መንገድ የተነሱ ሲሆን ማህተም አላስረከብም በማለት ማቅን ተተግነው በህገ ወጥ መንገድ እየሰሩ መሆናቸውነ ከዚህ በፊት የዘገብን መሆኑ ይታወሳል፡፡

No comments:

Post a Comment