Tuesday, August 21, 2012

ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ አረፉ


ኢትዮጵያን ለ21 ዓመታት የመሩት ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ አረፉ፡፡ ላለፉት ከ28 ዓመታት በመሪነት ቦታ ላይ የቆዩት ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ህይወታቸው ዕረፍት አልባ እንደነበር እና በቀንም ሁለት ሰዓት ቢበዛ ሶስት ሰዓት ብቻ በእንቅልፍ ያሳልፉ እንደነበር ይነገራል፡፡
የጠቅላይ ሚኒስቴሩ ሞት  ለሀገራችን ኢትዮጵያ ከባድ ሸክም ነው፡፡ ለብዙ የሀገሪቱ እቅዶች ባለራዕይ የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስቴሩ የኢትዮጵያን ገጽታ በዓለም አቀፍ ደረጃ የለወጡ እና አለማቀፍ ተቀባይነትዋን የጨመሩ ታላቅ መሪ ነበሩ፡፡
አገራችን ታላቅ መሪዋን አትጣለች፡፡ ለህዝቦችዋ ሁሉ መጽናናት ይሁንላቸው፡፡ አውደ ምህረትም የተሰማትን ጥለቅ ሀዘን ትገልጻለች፡፡

No comments:

Post a Comment