Sunday, August 12, 2012

ማን ይግዛን?

Click here to read in PDF: man yigzan
ምንጭ፡-ቤተ ጳውሎስ
መሪ መፈለግ የሰው ልጅ የተፈጥሮ ጠባይ ነው፡፡ ሕዝብ አንድ ድምጽ ኖሮት እንዲተዳደርናጠላቱን እንዲከላከል መሪ ያስፈልገዋል፡፡ መሪ የነጻነት ምልክት ነው፡፡ ሕዝቡን ቢበጅም ባይበጅምንጉሥ ያላት አገር ነጻነት እንዳላት ይታወቃል፡፡ መሪነት ከእግዚአብሔር የሚሰጥ ስጦታ  ነው/ምሳ.8፡15/፡፡ መሪ ለመሆን ግን የሚያስፈልገው ቀድሞ ማየት ነው፡፡ ቀድሞ ያላየ መሪ መሆንአይችልም፡፡ የሥልጣን ሥርዓት የእግዚአብሔር ሥርዓት ነው/ሮሜ.13፡1-7/፡፡ ገዥና ተገዢ መሆንግን የሥራ ድርሻ እንጂ የስብእና ልዩነት አይደለም፡፡ በዘመናት መሪዎች ሕዝቡ ለእነርሱ እንደተፈጠረ ያስቡ ነበር፡፡ የእግዚአብሔር ፈቃድ ግን መሪው የሕዝቡ እንጂ ሕዝቡ የመሪው እንዲሆንአይደለም/2ሳሙ.23፡3-4፤1ነገ.12፡7፤1ጴጥ.5፡2-3/፡፡
ሕዝብ በሌለበት ወንበር አይኖርም፣ ሕዝብ ባለበትም መሪ አይቀርም፡፡ ሁላችንም እኩል ነንየሚሉ ወገኖች እንኳን ስያሜውን አይቀበሉት እንጂ መሪ አላቸው፡፡ ሥራው ካለ ስያሜው ትንሽድርሻ ነው የሚወስደው፡፡ ሥልጣን የገዢዎች ደሴት አይደለም፡፡ ስለዚህ የመንግሥትና የሕዝብየሚባል ነገር አይኖርም፡፡ የመንግሥት የሕዝብ ነው፣ የሕዝብም የመንግሥት ነው፡፡ ምክንያቱምሁለቱም አንዱ የአንዱ ነውና፡፡

ይህ ሲሆን ነው ሥራ የሚሠራው፡፡  ኅብረት ማለት አንድ የጋራ ነገርን በእኩል መጠቀምናአንዱ የአንዱ እስኪሆን ድረስ ራስን መካድ ወይም መሞት  መሆኑን ቃሉ ይነግረናል፡፡
መሪን መውደድ ጸጋ ነው፡፡ ለመውደድ ግን መውደድ እንጂ ምንም ቅድመ ሁኔ ዎችየሉትም፡፡ ለመሪዎች መጸለይ ግድ ነው፡፡ ምክንያቱም በፀጥታ  መኖር የምንችለው ለእነርሱ በትጋትስንጸልይ ነው/1ጢሞ.2፡1/፡፡ ጳውሎስ ለንጉሥ በብርቱ መጸለይን ሲናገር በዘመኑ የነበረው ንጉሥኔሮን ቄሣር መሆኑን መዘንጋት የለብንም፡፡ ኔሮን በጭካኔው ወደር ያልነበረው የክርስትና አሳዳጅናከሦስት ዓመት በኋላ ጳውሎስን የሚሰይፈው ቢሆንም ሊጸለይለት ይገባ ነበር፡፡ ስንጸልይእግዚአብሔር በፍቅር ይነካቸዋል፡፡ ለመሪዎች መጸለይ ካልቻልን ሰይጣን ሲያውካቸው ሕዝቡንያውካሉ፡፡
መሪዎች እጅግ ፍቅር የሚያስፈልጋቸውና ፍቅርን የተራቡ ናቸው፡፡ ከመቼውም ጊዜ ይልቅሕዝቦች መሪዎቻቸውን ይጠላሉ፡፡ ማንም የመጥላት መብቱ ዲሞክራሲ የሚባል የምድር ሕግቢሆንም ክርስትና ግን የማፍቀርን መብት የሚጠቀም ሰማያዊ ሕግ ነው፡፡ ማፍቀር ሲቻል መጥላትእንዴት ይመረጣል? ሰዎች ነጻነት አላችሁ በተባሉበት አገር ሁሉ ነጻነታቸውን ጥላቻቸውንለመግለጥ መጠቀማቸው በመሪዎችና በሕዝብ መካከል ረጅም ገደል ፈጥሯል።
በዓለማችን ላይ ብዙ ገዥዎች ተለዋውጠዋል፡፡ ከአውሬ በጥቂት የሚለዩ አምባገነኖችምተከስተዋል፡፡ ደጋግ ነገሥታትም ራቅ ራቅ ብለው ተነሥተዋል፡፡ የእነዚህ ደጋግ ነገሥታትምንጫቸው ጥሩ ስብእናቸው ሳይሆን ስብእናን የሚለውጠው የእግዚአብሔር ፍቅር ነበር፡፡ ሥልጣንየሕዝብ አደራ መሆኑን መቀበል ከብልግና አያግድም፡፡ ሥልጣን የእግዚአብሔር አደራ መሆኑንመቀበል ግን ጠንቃቃ ያደርጋል፡፡ የክፉ ገዢዎች ተጽእኖም አሁን ያሉበት ወንበር ሳይሆን ያደጉበትቤተሰብና  ኅብረተሰብ የነፈጋቸው ፍቅር ነው፡፡ ማንም ቢሆን ያልተቀበለውን አይሰጥም፡፡
 እግዚአብሔር በተናቁ ሰዎች ዓለምን የሚያናውጥ ሥራ ይሠራል፡፡ በማይገመቱሰዎች ፈዋሽ  ታሪክ መሥራት ባሕርይው ነው፡፡ ሰይጣን ግን በትልልቅና በዝነኛ ሰዎችይጠቀማል፡፡ በቀላሉ ሥራው ይከናወንለታልና፡፡ ስለዚህ ለአገርና ለቤተ ክርስቲያን መሪዎችበብርቱ የምንጸልየው ሰይጣን ዒላማ ስለሚያደርጋቸውና በቀላሉም ብዙ ጥፋት ሊከሰት ስለሚችልነው፡፡
        በዓለማችን ላይ በእግዚአብሔር ሳይሆን በክንዳቸው የሚተማመኑ ነገሥታት ተፈራርቀዋል፡፡በአሁኑ ጊዜ ያሉት የምድር ነገሥታት በሙሉ በአፋቸው የእግዚአብሔር ስም የማይገባ ሃይማኖትየለሽ መሪዎች ናቸው፡፡ ስለዚህ ለገዛ ሕጋቸው እንኳን መታዘዝ እያቃታቸው ራሳቸውን እየተቃወሙየሚኖሩ፣ ውሸትን በኃይል እውነት ለማድረግ የሚጥሩ ሆነዋል፡፡ እነዚህ ነገሥታት እምነትንባይፈልጉም ሃይማኖትን ግን የሥልጣናቸው ሞግዚት ለማድረግ ይጠቀሙበታል፡፡ እግዚአብሔርየሌለው ሰው ለክፋቱ ምን ከልካይ ይኖረዋል?
ሥልጣን ዐጽመ ርስት መሆኑ ቀርቶ ሥልጣን ከቤተሰብ ወደ ሕዝብ መጥቷል፡፡ ከሕዝብምወደ ቅኖች ሳይሆን ማድረግን በንግግር ተክተው ወደሚኖሩ የአንደበት  ኃይሎች አጋድሏል፡፡በምኞት ሕብስተ መና እንሰጣችኋለን ያሉትም የተለመደውን ኑሮ እንኳ ሲያደፈርሱት በታሪክአይተናል፡፡ ከተጨነቀችው ዓለም ጋር የተጨነቀችው ኢትዮጵያ ፊውዳሊዝምን፣ ሶሻሊዝምን፣ካፒታሊዝምን መፍትሔ ቢሆን ብላ አስተናግዳለች፡፡ ዛሬም ከእነዚህ የተለየ የፖለቲካ ራእይ አሳዩኝትላለች፡፡ የኢትዮጵያ መልሱ ግን እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡
የእስራኤል ልጆች ብርቱ ጠላታቸው ከነበሩት ከምድያም እጅ ጌዴዎን ከታደጋቸው በኋላእንዲህ አሉት፡- ከምድያም እጅ አድነኸናልና አንተ ልጅህም የልጅ ልጅህም ደግሞ ግዙንአሉት፡፡ ጌዴዎንም፡- እኔ አልገዛችሁም ÷ልጄም አይገዛችሁም፤ እግዚአብሔር ይገዛችኋልአላቸው” /መሳ.8÷22-23/፡፡ እኛስ ኢትዮጵያውያን ማን ይግዛን?  እግዚአብሔር በጽድቅይግዛን!*

No comments:

Post a Comment